🔇Unmute
ሐረር ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡-በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ዘርፉን ለማበረታታት ድጋፍና ክትትሉን ማጠናከሩን የክልሉ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ገለጸ።
የክልሉ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ሃምዲ ሰላህዲን ለኢዜአ እንደተናገሩት በክልሉ የኢንቨስትመንት ዘርፉን ለማበረታታት የድጋፍና ክትትል ስራ ትኩረት ተሰጥቶታል።
በዚህም በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያው ሩብ ዓመት 1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ 32 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፍቃድ መሰጠቱን ጠቅሰዋል።
የኢንቨስትመንት ፍቃድ የተሰጣቸውም በግብርና፣ በማኑፋክቸሪንግ እና በአገልግሎት ዘርፎች መሆኑን ተናግረዋል።
የኢቨስትመንት ስራውን ውጤታማነት ለማሳደግ የድጋፍና ቁጥጥር ስራዎችን በማጠናክር በተገቢው ወደ ስራ ያልገቡ 40 አልሚዎች ላይ ከማስጠንቀቂያ ጀምሮ እስከ ኢንቨስትመንት ፍቃድ የመሰረዝ እርምጃ መወሰዱን አመልክተዋል።
እርምጃ ከተወሰደባቸው ባለሐብቶች መካከል 17ቱ በገቡት ውል መሠረት ያላለሙ እና መሬት ተረክበው ወደ ስራ ያልገቡ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ሌሎች ያለ በቂ ምክንያት ግንባታ ያቋረጡና ያለ ግንባታ ፈቃድ ስራ የጀመሩ 18 አልሚዎች ደግሞ እንዲታገዱ መደረጉን ገልጸዋል።
ከዚህ በተጨማሪ የተለያዩ የድጋፍ ስራዎች ተደርጎላቸው እና መሬት ተረክበው አጥረው በተቀመጡ የአምስት አልሚዎች ፍቃድ መሰረዙን ገልጸዋል።
በቀጣይም በኢንቨስትመንት ፍቃድ መሬት ወስደው ወደ ስራ ያልገቡ አልሚዎች ላይ ክትትል በማድረግ ተገቢውን እርምጃ የመውሰዱ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025