🔇Unmute
ሐረር ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡-በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ዘርፉን ለማበረታታት ድጋፍና ክትትሉን ማጠናከሩን የክልሉ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ገለጸ።
የክልሉ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ሃምዲ ሰላህዲን ለኢዜአ እንደተናገሩት በክልሉ የኢንቨስትመንት ዘርፉን ለማበረታታት የድጋፍና ክትትል ስራ ትኩረት ተሰጥቶታል።
በዚህም በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያው ሩብ ዓመት 1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ 32 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፍቃድ መሰጠቱን ጠቅሰዋል።
የኢንቨስትመንት ፍቃድ የተሰጣቸውም በግብርና፣ በማኑፋክቸሪንግ እና በአገልግሎት ዘርፎች መሆኑን ተናግረዋል።
የኢቨስትመንት ስራውን ውጤታማነት ለማሳደግ የድጋፍና ቁጥጥር ስራዎችን በማጠናክር በተገቢው ወደ ስራ ያልገቡ 40 አልሚዎች ላይ ከማስጠንቀቂያ ጀምሮ እስከ ኢንቨስትመንት ፍቃድ የመሰረዝ እርምጃ መወሰዱን አመልክተዋል።
እርምጃ ከተወሰደባቸው ባለሐብቶች መካከል 17ቱ በገቡት ውል መሠረት ያላለሙ እና መሬት ተረክበው ወደ ስራ ያልገቡ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ሌሎች ያለ በቂ ምክንያት ግንባታ ያቋረጡና ያለ ግንባታ ፈቃድ ስራ የጀመሩ 18 አልሚዎች ደግሞ እንዲታገዱ መደረጉን ገልጸዋል።
ከዚህ በተጨማሪ የተለያዩ የድጋፍ ስራዎች ተደርጎላቸው እና መሬት ተረክበው አጥረው በተቀመጡ የአምስት አልሚዎች ፍቃድ መሰረዙን ገልጸዋል።
በቀጣይም በኢንቨስትመንት ፍቃድ መሬት ወስደው ወደ ስራ ያልገቡ አልሚዎች ላይ ክትትል በማድረግ ተገቢውን እርምጃ የመውሰዱ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026