🔇Unmute
ሐረር ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡-በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ዘርፉን ለማበረታታት ድጋፍና ክትትሉን ማጠናከሩን የክልሉ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ገለጸ።
የክልሉ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ሃምዲ ሰላህዲን ለኢዜአ እንደተናገሩት በክልሉ የኢንቨስትመንት ዘርፉን ለማበረታታት የድጋፍና ክትትል ስራ ትኩረት ተሰጥቶታል።
በዚህም በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያው ሩብ ዓመት 1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ 32 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፍቃድ መሰጠቱን ጠቅሰዋል።
የኢንቨስትመንት ፍቃድ የተሰጣቸውም በግብርና፣ በማኑፋክቸሪንግ እና በአገልግሎት ዘርፎች መሆኑን ተናግረዋል።
የኢቨስትመንት ስራውን ውጤታማነት ለማሳደግ የድጋፍና ቁጥጥር ስራዎችን በማጠናክር በተገቢው ወደ ስራ ያልገቡ 40 አልሚዎች ላይ ከማስጠንቀቂያ ጀምሮ እስከ ኢንቨስትመንት ፍቃድ የመሰረዝ እርምጃ መወሰዱን አመልክተዋል።
እርምጃ ከተወሰደባቸው ባለሐብቶች መካከል 17ቱ በገቡት ውል መሠረት ያላለሙ እና መሬት ተረክበው ወደ ስራ ያልገቡ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ሌሎች ያለ በቂ ምክንያት ግንባታ ያቋረጡና ያለ ግንባታ ፈቃድ ስራ የጀመሩ 18 አልሚዎች ደግሞ እንዲታገዱ መደረጉን ገልጸዋል።
ከዚህ በተጨማሪ የተለያዩ የድጋፍ ስራዎች ተደርጎላቸው እና መሬት ተረክበው አጥረው በተቀመጡ የአምስት አልሚዎች ፍቃድ መሰረዙን ገልጸዋል።
በቀጣይም በኢንቨስትመንት ፍቃድ መሬት ወስደው ወደ ስራ ያልገቡ አልሚዎች ላይ ክትትል በማድረግ ተገቢውን እርምጃ የመውሰዱ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026