የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በምዕራብ ጎንደር ዞን ግማሽ ሚሊዮን ቶን የሚጠጋ የእንስሳት መኖ ተሰበሰበ

Nov 3, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ገንዳውኃ፤ ጥቅምት 22/2018 (ኢዜአ):-በምዕራብ ጎንደር ዞን የእንስሳት ምርታማነትን ይበልጥ ለማሳደግ የሚያግዝ ግማሽ ሚሊዮን ቶን የሚጠጋ መኖ መሰብሰቡን የዞኑ እንስሳትና አሣ ሃብት ተጠሪ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።

በጽሕፈት ቤቱ የእንስሳት ተዋፅኦ ምርት ባለሙያ አቶ ወርቄ ዱቤ፤ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብሩ ለእንስሳት ጤና አጠባበቅና ምርታማነት ትኩረት እንዲሰጥ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ለኢዜአ ተናግረዋል።

በዚህም በበጀት ዓመቱ በአካባቢው ከሚገኘው የሣር ድርቆሽና ከኢንዱስትሪ ውጤቶች ከ2 ነጥብ 3 ሚሊዮን ቶን በላይ መኖ ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

እስካሁን በተደረገው ጥረትም ግማሽ ሚሊዮን ቶን የሚጠጋ መኖ በመሰበሰብ ማከማቸት መቻሉን አስታወቀዋል።

ይህም የእንስሳት ጤናን በመጠበቅ በበጀት ዓመቱ ከ121 ሚሊዮን ሊትር በላይ ወተትና ከ12ሺህ 540 ቶን በላይ ሥጋ ለማምረት የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት እንደሚያግዝ አስረድተዋል።

እስካሁንም ከ22 ሚሊዮን ሊትር በላይ ወተትና ከአንድ ሺህ 774ቶን በላይ ሥጋ በማምረት ለቤት ውስጥ ፍጆታና ለአካባቢው ማህብረሰብ በማቅረብ አርሶ አደሩ ተጠቃሚ ሆኗል ብለዋል።

እንደ ባለሙያው ገለጻ ፤ በዞኑ በሚገኙ ወረዳዎች ለእንስሳት እርባታ ምቹና ለመኖ ልማት የሚውል መሬት መኖሩ የወተትና የሥጋ ምርትን ለመጨመር እያስቻለ ነው።

በአካባቢው የተሻለ የሥጋና የወተት ምርት የሚሰጡ የዳልጋ ከብት ዝርያዎችን በዘመናዊ መንገድ በማባዛት ለአርሶ አደሩ ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።

በዞኑ ገንዳውኃ ከተማ በእንስሳት እርባታ ሥራ ላይ ከተሰማሩት ነዋሪዎች መካከል አቶ ቢሰጥ ካሴ በሰጡት አስተያየት፤ በአካባቢው የመኖ ልማትን በዘመናዊ መንገድ አከማችተው ላሞቻቸውን እየቀለቡ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በዚህም ቀደም ሲል ከአንድ ላም ያገኙት የነበረውን ከአንድ ሊትር ያልበለጠ የወተት ምርት ወደ ሦስት ሊትር በማሳደግ ተጠቃሚ እንደሆኑ ገልጸዋል።

በዞኑ ቋራ ወረዳ የገለጎ ከተማ ነዋሪ አቶ አየነው እሸቴ በበኩላቸው፤ የወተት ላሞችን ጤና አጠባበቅና የመኖ አቅርቦትን በማሻሻል በወተት ምርት ተጠቃሚነታቸው እያደገ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026