የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በምዕራብ ሐረርጌ ዞን በመኽር አዝመራ በተካሄደ በርበሬ ልማት ከ720 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ይጠበቃል

Nov 6, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ጭሮ ፣ጥቅምት 26/2018 (ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሐረርጌ ዞን በመኽር ወቅቱ ከለማው በርበሬ ከ720 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ የዞኑ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡

በጽህፈት ቤቱ የቡና ሻይ እና ቅመማ ቅመም ልማት ቡድን መሪ አቶ ኦሉማ በዳኔ እንዳሉት በዞኑ በመኸር አዝመራ በ15 ወረዳዎች 34 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ በርበሬ ለምቷል።

በዞኑ ምርቱ በስፋት በሚካሄድባቸው የሀዊ ጉዲና ፤ ጭሮ፤ ዳሮ ለቡ፤ ገመቺስ ፤ሀብሮ ፤ኦዳ ቡልቱም እና ቦኬ ወረዳዎች የምርት ስብሰባ እየተካሄደ መሆኑን ነው የገለጹት፡፡

በዚህ ዓመት ይገኛል ተብሎ የሚጠበቀው ምርት ካለፈው ዓመት ከአስር ሺህ ኩንታል በላይ ብልጫ እንደሚኖረው ነው ያመለከቱት፡፡

በዞኑ የበርበሬ አኒሼቲቭን ለማሳካት አርሶአደሩ ልማቱን በክላስተር በማልማት በጋራ እንዲሳተፍ ስራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል፡፡

አርሶአደሮች ለምርት ጥበቃና እንክብካቤ ትኩረት እንዲሰጡ በተደረገው ድጋፍና ክትትል በሄክታር የምርታማነት መጠኑን ከ16 ኩንታል ወደ 20 ኩንታል ያድጋል ተብሎ እንደሚጠበቅም አመልክተዋል፡፡

በምዕራብ ሐረርጌ ዞን 15 ወረዳዎች እየተካሄደ ባለው የበርበሬ ልማት ከ55 ሺህ በላይ አርሶአደሮች እየተሳተፉ መሆኑም ተመልክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025