የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በክልሉ በበጋ መስኖ የግብርና ልማት ስራ ከ148 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች ይለማል

Nov 7, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ሆሳዕና ፤ ጥቅምት 27/2018(ኢዜአ)፡- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በበጀት ዓመቱ በበጋ መስኖ ግብርና ልማት ከ148 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች ለማልማት ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለፀ፡፡

የክልሉን የበጋ ወቅት የመስኖ ልማት ስራ በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የቢሮው ምክትል ኃላፊና የእርሻና ሆርቲካልቸር ዘርፍ ኃላፊ አቶ አለምይርጋ ወልደስላሴ እንደገለፁት፡- በክልሉ በበጋ መስኖ ከ148 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች ለመሸፈን ታቅዶ ወደ ተግባር ተገብቷል፡፡


በአብዛኛው በሆርቲካልቸር ሰብሎች ላይ በማተኮር እንደሚሰራ ተናግረው ከ37 ነጥብ 3 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ግብ ተጥሎ ወደ ተግባር ስለመገባቱም ተናግረዋል፡፡

ለዚህም ስኬት ከክልል እስከ ወረዳ በሚገኙ መዋቅሮች የንቅናቄና የተግባቦት መድረክ ተፈጥሮ ወደ ትግበራ ምዕራፍ ስለመገባቱም ነው ያስረዱት፡፡

የመኸር ምርት መሰብሰብ የተጀመረባቸው አካባቢዎች የእርሻ ስራን ጨምሮ ለበጋ መስኖ ግብርና ስራው ትግበራ የሚረዱ ድጋፎች እየተደረገ እንደሚገኝም ገልፀዋል፡፡

በክልሉ በሁለት ዙር በሚለማው የበጋ መስኖ ግብርና ልማት ስራ ያሉትን የውሃ አማራጮች ለመጠቀም የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት ተደርጎ ወደ ተግባር ስለመገባቱም ነው ኃላፊው የተናገሩት፡፡

የስልጤ ዞን ግብርና መምሪያ ምክትል ኃላፊና የእርሻ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሳዲቅ አህመዲን በበኩላቸው ፡በዘንድሮው የበጋ መስኖ ግብርና ልማት ስራ ከ16 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች በመሸፈን ከ 4 ነጥብ 1 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት ታቅዷል ብለዋል፡፡


በዞኑ ያሉትን የውሃ አማራጮች ከመጠቀም በተጨማሪ አርሶ አደሩ ድረስ በመዝለቅ በቂ መግባባት ተፈጥሮ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው ምርት መሰብሰብ በተጀመረባቸው አካባቢዎች 4 ሺህ ሄክታር መሬት መታረሱንም ገልፀዋል።

በሀላባ ዞን ዌራ ዲጆ ወረዳ በግል የእርሻ ልማት ስራ የተሰማራ ድርጅት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ስዩም ኃይለጊዮርጊስ በበጋ መስኖ ልማት ስራ የተለያዩ ሰብሎችን ለማልማት ታቅዶ የመሬት ዝግጅትን በማጠናቀቅ ወደ ዘር ስራ እየተገባ መሆኑን ተናግረዋል።


በተለይም የአትክልትና የቅባት እህሎችን ጨምሮ ስንዴን በበጋ መስኖ በማልማት ለሀገር ውስጥ ፍጆታና ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ሰብሎችን በስፋትና በጥራት ለማምረት እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026