የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ሁለንተናዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ የጎላ ሚና ይጫወታል

Nov 10, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሕዳር 1/2018(ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ሁለንተናዊ ዕድገት እና ልማትን ለማስቀጠል ብሎም ቀጣናዊ ሚናን ለማጉላት ወሳኝ ሚና እንዳለው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ብዙአየሁ ደገፋ (ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቅርቡ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ማብራሪያ፣ የቀይ ባህር ጉዳይ ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓ ምድራዊ (ጂኦግራፊያዊ) እና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ መሆኑን አስረድተዋል።

የቀይ ባሕር ባለቤትነትን ጥያቄ ለመፍታት የተረጋጋ፣ የሰከነና በውይይት ላይ የተመሰረተ አካሄድ መከተል እንደሚያስፈልግ አመልክተው፣ ለማጣት የፈጀውን ያህል ለመመለስ አይፈጅም ብለዋል።

ኢትዮጵያ የባሕር በር ያጣችበት መንገድም ሕጋዊና ተቋማዊ መሠረት የሌለው የሚያስቆጭ የብሔራዊ ጥቅም ስብራት አካል መሆኑን አስረድተዋል።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ብዙአየሁ ደገፋ (ዶ/ር)፤ ኢትዮጵያ የባሕር በር ያጣችበት መንገድ፣ ሕጋዊና ታሪካዊ ቅቡልነት የሌለው ሴራ ነው ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ሁለንተናዊ እድገትን ለማስቀጠል ያለመ መሆኑን ገልጸው፤ ቀጣናዊ የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት እያገኘ መምጣቱን ጠቁመው፤ የጀመረችውን የለውጥ ጉዞ ከዳር ለማድረስ ብሎም ለሀገር ዕድገትና ልማት ወሳኝ መሆኑን አስምረውበታል።

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤት መሆን ከራሷ አልፋ ጎረቤት ሀገራትንና ቀጣናውን እንድትደግፍ የሚያስችላት መሆኑን ጠቁመው፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለቀጣናዊ ትብብርና የኃይል ልማት እያበረከተ ያለውን አስተዋጽኦ ለአብነት አንስተዋል።

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት የቀጣናውን ሀገራት አብሮ የማደግ ዕድል የሚያሰፋ መሆኑንም እንዲሁ፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026