🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 1/2018(ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ሁለንተናዊ ዕድገት እና ልማትን ለማስቀጠል ብሎም ቀጣናዊ ሚናን ለማጉላት ወሳኝ ሚና እንዳለው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ብዙአየሁ ደገፋ (ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቅርቡ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ማብራሪያ፣ የቀይ ባህር ጉዳይ ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓ ምድራዊ (ጂኦግራፊያዊ) እና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ መሆኑን አስረድተዋል።
የቀይ ባሕር ባለቤትነትን ጥያቄ ለመፍታት የተረጋጋ፣ የሰከነና በውይይት ላይ የተመሰረተ አካሄድ መከተል እንደሚያስፈልግ አመልክተው፣ ለማጣት የፈጀውን ያህል ለመመለስ አይፈጅም ብለዋል።
ኢትዮጵያ የባሕር በር ያጣችበት መንገድም ሕጋዊና ተቋማዊ መሠረት የሌለው የሚያስቆጭ የብሔራዊ ጥቅም ስብራት አካል መሆኑን አስረድተዋል።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ብዙአየሁ ደገፋ (ዶ/ር)፤ ኢትዮጵያ የባሕር በር ያጣችበት መንገድ፣ ሕጋዊና ታሪካዊ ቅቡልነት የሌለው ሴራ ነው ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ሁለንተናዊ እድገትን ለማስቀጠል ያለመ መሆኑን ገልጸው፤ ቀጣናዊ የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ መሆኑን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት እያገኘ መምጣቱን ጠቁመው፤ የጀመረችውን የለውጥ ጉዞ ከዳር ለማድረስ ብሎም ለሀገር ዕድገትና ልማት ወሳኝ መሆኑን አስምረውበታል።
የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤት መሆን ከራሷ አልፋ ጎረቤት ሀገራትንና ቀጣናውን እንድትደግፍ የሚያስችላት መሆኑን ጠቁመው፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለቀጣናዊ ትብብርና የኃይል ልማት እያበረከተ ያለውን አስተዋጽኦ ለአብነት አንስተዋል።
የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት የቀጣናውን ሀገራት አብሮ የማደግ ዕድል የሚያሰፋ መሆኑንም እንዲሁ፡፡
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026