የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ሀዋሳ ከተማን ለመኖሪያ፣ ለቱሪዝምና ለኮንፈረንስ ተመራጭ ለማድረግ ይሰራል-ከንቲባ ጥራቱ በየነ

Nov 13, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦ሀዋሳ ከተማን ለመኖሪያ፣ ለቱሪዝምና ለኮንፈረንስ ተመራጭ ከተማ ለማድረግ ከፍ ያለ ራዕይ በመሰነቅ ይሰራል ሲሉ አዲሱ የከተማዋ ከንቲባ ጥራቱ በየነ ገለጹ።

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 2ኛ ዙር አስረኛ ዓመት 2ኛ አስቸኳይ ጉባኤ አቶ ጥራቱ በየነን የከተማዋ ከንቲባ አድርጎ ሾሟል።


አዲሱ የከተማዋ ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ ለምክር ቤቱ አባላት ባደረጉት ንግግር እንዳሉት፤ ከተሞችን የብልጽግና ማሳያ ለማድረግ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት በአዲስ እሳቤ የተጀመረው የኮሪደር ልማት በሀዋሳ ከተማም እየተከናወነ ነው።

በከተማዋ የተጀመሩ የልማት ሥራዎችን አጠናክሮ በማስቀጠል ሀዋሳን ከአዲስ አበባ በመቀጠል በኢትዮጵያ ብሎም በአፍሪካ ለመኖሪያ፣ ቱሪዝምና ለኮንፈረንስ ተመራጭ ለማድረግ ከፍ ያለ ራዕይ ሰንቀን ያለመዘናጋት እንሰራለን ብለዋል።

ለዚህ ራዕይ ስኬት የመንግስት፣ የነዋሪውና የግል ሴክተሩ የተቀናጀና የተናበበ ስራ ወሳኝ መሆኑን ያነሱት አቶ ጥራቱ ሁሉንም ማህበረሰብ በማሳተፍ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።

የሀዋሳን በፍቅር ተከባብሮና ተደጋግፈው በወንድማማችነትና በአንድነት የሚኖሩባት የፍቅር ከተማነቷን ለማስቀጠል ጠንክረው እንደሚሰሩም ጠቁመዋል።


የከተማዋን ሰላምና ጸጥታ አጠናክሮ በማስቀጠል ለነዋሪዎቿ ምቹ ከተማ እንድትሆን ለማድረግ ህብረተሰቡን ያሳተፈ የሰላምና ጸጥታ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል።

ዓለም አቀፍ መስፈርቶችንና የከተማ ፕላንን መሰረት ባደረገ መልኩ በከተማዋ መሰረተ ልማቶችንና አረንጓዴ ስፍራዎችን የማስፋፋት ሥራ እንደሚሰራ ገልጸው፣ የሀዋሳ ሐይቅን ከብክለት የመጠበቅና የታቦር ተራራን ልማት በማፋጠን ለጎብኚዎች ምቹ የማድረግ ስራ ይሰራል ብለዋል።

የቆሻሻ አወጋገድና አያያዝን ከማዘመን ባለፈ ዘላቂ የከተማ ልማትን ተግባራዊ በማድረግ ንጹህና ምቹ ሀዋሳን ለመፍጠርም ትኩረት እንደሚሰጥ አመልክተዋል።

ሀዋሳ ከተማን ተመራጭ የቱሪዝምና የኮንፈረንስ መዳረሻ ለማድረግም ደረጃቸውን የጠበቁ የቱሪስት መዳረሻዎችን ቁጥር ከማሳደግ ባለፈ የከተማዋን የቱሪስት ሀብቶች ለማስተዋወቅ በትኩረት እንደሚሰራም አስታውቀዋል።

ከንቲባው በከተማዋ የኑሮ ውድነትን ለማቃለል የተጀመሩ የከተማ ግብርና የሌማት ትሩፋት መርሀግብሮች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።


በስራ ዕድል ፈጠራ ለግሉ፤ ኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ሴቶች ወጣቶችና የተለያዩ ወገኖች ተጠቃሚ እንዲሆኑ በማድረግ የስራ አጥነትን ጫና ለማቃለል እንደሚሰራም አቶ ጥራቱ አስታውቀዋል።

የከተማ አስተዳደሩ ምክር ቤት በብልጽግና ፓርቲ የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ አብርሀም ማርሻሎ የቀረበለትን የአቶ ጥራቱ በየነን የከንቲባነት ሹመት በሙሉ ድምጽ ተቀብሎ በማጽደቅ ጉባኤውን አጠናቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026