የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ሀዋሳ ከተማን ለመኖሪያ፣ ለቱሪዝምና ለኮንፈረንስ ተመራጭ ለማድረግ ይሰራል-ከንቲባ ጥራቱ በየነ

Nov 13, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦ሀዋሳ ከተማን ለመኖሪያ፣ ለቱሪዝምና ለኮንፈረንስ ተመራጭ ከተማ ለማድረግ ከፍ ያለ ራዕይ በመሰነቅ ይሰራል ሲሉ አዲሱ የከተማዋ ከንቲባ ጥራቱ በየነ ገለጹ።

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 2ኛ ዙር አስረኛ ዓመት 2ኛ አስቸኳይ ጉባኤ አቶ ጥራቱ በየነን የከተማዋ ከንቲባ አድርጎ ሾሟል።


አዲሱ የከተማዋ ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ ለምክር ቤቱ አባላት ባደረጉት ንግግር እንዳሉት፤ ከተሞችን የብልጽግና ማሳያ ለማድረግ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት በአዲስ እሳቤ የተጀመረው የኮሪደር ልማት በሀዋሳ ከተማም እየተከናወነ ነው።

በከተማዋ የተጀመሩ የልማት ሥራዎችን አጠናክሮ በማስቀጠል ሀዋሳን ከአዲስ አበባ በመቀጠል በኢትዮጵያ ብሎም በአፍሪካ ለመኖሪያ፣ ቱሪዝምና ለኮንፈረንስ ተመራጭ ለማድረግ ከፍ ያለ ራዕይ ሰንቀን ያለመዘናጋት እንሰራለን ብለዋል።

ለዚህ ራዕይ ስኬት የመንግስት፣ የነዋሪውና የግል ሴክተሩ የተቀናጀና የተናበበ ስራ ወሳኝ መሆኑን ያነሱት አቶ ጥራቱ ሁሉንም ማህበረሰብ በማሳተፍ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።

የሀዋሳን በፍቅር ተከባብሮና ተደጋግፈው በወንድማማችነትና በአንድነት የሚኖሩባት የፍቅር ከተማነቷን ለማስቀጠል ጠንክረው እንደሚሰሩም ጠቁመዋል።


የከተማዋን ሰላምና ጸጥታ አጠናክሮ በማስቀጠል ለነዋሪዎቿ ምቹ ከተማ እንድትሆን ለማድረግ ህብረተሰቡን ያሳተፈ የሰላምና ጸጥታ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል።

ዓለም አቀፍ መስፈርቶችንና የከተማ ፕላንን መሰረት ባደረገ መልኩ በከተማዋ መሰረተ ልማቶችንና አረንጓዴ ስፍራዎችን የማስፋፋት ሥራ እንደሚሰራ ገልጸው፣ የሀዋሳ ሐይቅን ከብክለት የመጠበቅና የታቦር ተራራን ልማት በማፋጠን ለጎብኚዎች ምቹ የማድረግ ስራ ይሰራል ብለዋል።

የቆሻሻ አወጋገድና አያያዝን ከማዘመን ባለፈ ዘላቂ የከተማ ልማትን ተግባራዊ በማድረግ ንጹህና ምቹ ሀዋሳን ለመፍጠርም ትኩረት እንደሚሰጥ አመልክተዋል።

ሀዋሳ ከተማን ተመራጭ የቱሪዝምና የኮንፈረንስ መዳረሻ ለማድረግም ደረጃቸውን የጠበቁ የቱሪስት መዳረሻዎችን ቁጥር ከማሳደግ ባለፈ የከተማዋን የቱሪስት ሀብቶች ለማስተዋወቅ በትኩረት እንደሚሰራም አስታውቀዋል።

ከንቲባው በከተማዋ የኑሮ ውድነትን ለማቃለል የተጀመሩ የከተማ ግብርና የሌማት ትሩፋት መርሀግብሮች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።


በስራ ዕድል ፈጠራ ለግሉ፤ ኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ሴቶች ወጣቶችና የተለያዩ ወገኖች ተጠቃሚ እንዲሆኑ በማድረግ የስራ አጥነትን ጫና ለማቃለል እንደሚሰራም አቶ ጥራቱ አስታውቀዋል።

የከተማ አስተዳደሩ ምክር ቤት በብልጽግና ፓርቲ የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ አብርሀም ማርሻሎ የቀረበለትን የአቶ ጥራቱ በየነን የከንቲባነት ሹመት በሙሉ ድምጽ ተቀብሎ በማጽደቅ ጉባኤውን አጠናቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026