የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ

Nov 20, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሕዳር 8/2018 (ኢዜአ)፡-በአፋር ክልል ያለውን የአገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገለጹ።

የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ የክልሉን መሶብ (ኮራ) የአንድ ማዕከል አገልግሎት በሰመራ ሎጊያ ከተማ ስራ አስጀምረዋል።

በመርኃ ግብሩ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ፣ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር መኩሪያ ሀይሌ (ዶ/ር) እንዲሁም የፌደራል እና የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።



የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ በዚሁ ወቅት፤ ለአገልግሎቱ መጀመር አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋና አቅርበው፤ በቀጣይ በተለያዩ የክልሉ ከተሞች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ለማስፋፋት እንደሚሰራ ተናግረዋል።

በክልሉ ያለውን የአገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል፡፡

10ኛው የከተሞች ፎረም በሰመራ ሎጊያ ከተማ መከናወኑ ለከተማዋ ከፍተኛ መነቃቃት የፈጠረ መሆኑንም ጠቁመዋል።

የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ በበኩላቸው፤ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለከተሞች ብዙ ትርጉም አለው ብለዋል።


አገልግሎቱ ዜጎች የሚገባቸውን አገልግሎት በተቀላጠፈ ሁኔታ የሚያገኙበት መሆኑን ጠቅሰው፤ በሰመራ ሎጊያ የተገነባው የመሶብ ማዕከል የሚደነቅ ስራ መሆኑን ጠቁመዋል።

ማዕከሉ መልካም አስተዳደርን በማስፈን በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ከፍተኛ ለውጥ እንደሚያመጣ ተናግረዋል።

በተጨማሪም በአንድ ቦታ በርካታ አገልግሎት በመስጠት ለዜጎች እፎይታን የሚሰጥ መሆኑን ጠቁመዋል።



መሶብ የተሳለጠ ሰው ተኮር አገልግሎት የሚሰጥበት ማዕከል መሆኑን የገለጹት ደግሞ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽነር መኩሪያ ሀይሌ(ዶ/ር) ናቸው።


የመልካም አስተዳደር ችግሮችን የሚፈታ እንዲሁም የአገልግሎት ልህቀት ማሳያ መሆኑን ጠቁመዋል።

ማዕከሉ ዜጎች ከመንግስት የሚፈልጉትን አገልግሎት በተቀላጠፈ ሁኔታ የሚያገኙበት የኢትዮጵያ ማንሰራራት መገለጫ መሆኑን ተናግረዋል።

የአፋር ክልል በዚህ ረገድ ያቋቋመው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የሚደነቅ ስራ መሆኑን ገልጸው ኮሚሽኑ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025