
አዲስ አበባ፤ ጥር 1/2017(ኢዜአ)፡- ሀገር በቀል ህንጻ ተቋራጮች ከሀገር አልፎ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት አስታወቀ።
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ታምራት ሙሉ(ኢ/ር) ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት የኮንስትራክሽን ዘርፉ በቴክኖሎጂ የዘመነና ተወዳዳሪ እንዲሆን ኢንስቲትዩቱ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ነው።
በዘርፉ ላይ ተወዳዳሪና የሰለጠነ የሰው ሀይል ለማፍራት ለዘርፉ ባለሙያዎች፣ ተቋማትና ህንጻ ተቋራጮች የተለያዩ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች እየሰጠ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።
በተለይ በሀገር ውስጥ የሚገኙ የህንጻ ተቋራጮች በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የክህሎት፣ የእውቀትና የቴክኖሎጂ ክፍተትን ለመሙላት እየተሰራ ያለውን ስራ ለአብነት አንስተዋል።
ይህንን ተከትሎ የሀገር ውስጥ ህንጻ ተቋራጮች በሀገር ውስጥ ህንጻዎችን ጨምሮ እየተገነቡ በሚገኙ ሜጋ ፕሮጀክቶች ላይ እየተሳተፉ መሆኑን ተናግረዋል።
በአሁኑ ወቅት ለኢንዱስትሪው ሽግግርና የቴክኖሎጂ እድገት ከፍተኛ ሚና ባለው የቢውልዲንግ ኢንፎርሜሽን ሞዴል ወይም(BIM) ላይ የህንጻ ተቋራጮች፣ የዘርፉ ምሁራንና ኢንዱስትሪዎች በቴክኖሎጂው ዙርያ ግንዛቤ እንዲኖራቸው የማድረግና የማስተዋወቅ ስራ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል
የፕሮጀክት ማኔጅመንት ፕሮፌሽናል ትሬኒንግ የተሰኘው ስልጠናም ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸውና የሀገር ኢኮኖሚ ላይ ለውጥ የሚያመጡ እንደ ታላቁ ህዳሴ ግድብ የመሳሰሉ ፕሮጀክቶችን የሚመሩ ባለሙያዎችም ስልጠናውን እንዲወስዱ እየተደረገ ነው ብለዋል።
በዚህም ባለፉት ስድስት ወራት 89 ባለሙያዎች ስልጠናውን አጠናቀው አለም አቀፍ የፕሮጀክት ማኔጅመንት ማረጋገጫ ወረቀት መውሰዳቸውን አስታውቀዋል።
የኮንስትራክሽን ዘርፉ በቴክኖሎጂ የዘመነና ተወዳዳሪ እንዲሆን ኢንስቲትዩቱ የጥናትና ምርምር ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝም ገልጸዋል፡፡
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026