
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን (ዶ/ር) ገለጹ።
ዩኒቨርሲቲው ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሕዝባዊ ተሳተፎ ማስተባበሪያ ምክር ቤት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው "የአባይ ዘመን ትውልድ" በሚል መሪ የኪነ ጥበብ መድረክ በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ተካሂዷል።

በመድረኩ የግድቡን ሁለንተናዊ ጠቀሜታና ቀጣናዊ ትስስር የሚያወሱ የስነ ጽሁፍና ሙዚቃ ስራዎች ቀርበዋል።
የዩኒቨርሲቲው የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን (ዶ/ር) በወቅቱ እንደገለፁት ግድቡ መላው ኢትዮጵያዊያን አሻራቸውን ያሳረፉበትና የትውልዱ ኩራት ነው።
በትውልድ ቅብብሎሽ የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ለሚገኘው ሕዳሴ ግድብ የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።
ዩኒቨርሲቲው ግድቡ ለተፋሰሱ አገራት የሚሰጠውን ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ማህበረሰቡ እንዲገነዘብ ለማድረግ የጥናትና የምርምር ማዕከል ለመክፈት በዝግጅት ላይ መሆኑንም ጠቁመዋል።
የህዳሴ ግድብ ከኤሌክትሪክ ኃይል በተጨማሪ ለወደፊቱም ቱሪዝምን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎችን እንደሚያስገኝ ገልጸዋል።
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የማህበራዊ ዘርፍ አማካሪ አቶ ጌታቸው ፊሊጾስ በበኩላቸው ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ መሰረት የሚጥል ግዙፍ ፕሮጀክት መሆኑን ገልፀዋል።
ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የተለያዩ የገቢ ማሰባሰብያ ፕሮግሞችን በማዘጋጀት ዜጎች ግዴታቸውን እንዲወጡ እየተደረገ እንደሚገኝ የተናገሩት ደግሞ የክልሉ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ዳይሬክተር አቶ ለሜሳ ኔኖ ናቸው ።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026