የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

Feb 28, 2025

IDOPRESS

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን (ዶ/ር) ገለጹ።

ዩኒቨርሲቲው ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሕዝባዊ ተሳተፎ ማስተባበሪያ ምክር ቤት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው "የአባይ ዘመን ትውልድ" በሚል መሪ የኪነ ጥበብ መድረክ በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ተካሂዷል።


በመድረኩ የግድቡን ሁለንተናዊ ጠቀሜታና ቀጣናዊ ትስስር የሚያወሱ የስነ ጽሁፍና ሙዚቃ ስራዎች ቀርበዋል።

የዩኒቨርሲቲው የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን (ዶ/ር) በወቅቱ እንደገለፁት ግድቡ መላው ኢትዮጵያዊያን አሻራቸውን ያሳረፉበትና የትውልዱ ኩራት ነው።

በትውልድ ቅብብሎሽ የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ለሚገኘው ሕዳሴ ግድብ የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።

ዩኒቨርሲቲው ግድቡ ለተፋሰሱ አገራት የሚሰጠውን ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ማህበረሰቡ እንዲገነዘብ ለማድረግ የጥናትና የምርምር ማዕከል ለመክፈት በዝግጅት ላይ መሆኑንም ጠቁመዋል።

የህዳሴ ግድብ ከኤሌክትሪክ ኃይል በተጨማሪ ለወደፊቱም ቱሪዝምን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎችን እንደሚያስገኝ ገልጸዋል።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የማህበራዊ ዘርፍ አማካሪ አቶ ጌታቸው ፊሊጾስ በበኩላቸው ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ መሰረት የሚጥል ግዙፍ ፕሮጀክት መሆኑን ገልፀዋል።

ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የተለያዩ የገቢ ማሰባሰብያ ፕሮግሞችን በማዘጋጀት ዜጎች ግዴታቸውን እንዲወጡ እየተደረገ እንደሚገኝ የተናገሩት ደግሞ የክልሉ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ዳይሬክተር አቶ ለሜሳ ኔኖ ናቸው ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026