የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

Feb 28, 2025

IDOPRESS

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመሆናቸው ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ መሸጋገራቸውን ገለጹ።


አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ አንቀሳቃሾች መካከል በሚዛን አማን ከተማ ከሁለት ዓመት በፊት በጫኝ አውራጅ ሥራ 23 አባላትን ይዞ የተደራጀውና ወደሥራ የገባው "ጥምረት ማኅበር" አንዱ ነው።


የማህበሩ ሰብሳቢ ወጣት ፓርቲ አርዱ እንደገለጸው፥ ማህበሩ ከ1 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር በላይ በመቆጠብ በአሁኑ ወቅት ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝነት አድጓል።


የማህበሩ አባላት በራሳቸው ፍላጎት ሽግግር ያደረጉት በአራት የተለያዩ የሥራ ዘርፎች በመሰማራት መሆኑን ጠቅሶ "ፍቅር የደረቅ እንጀራ ማኅበር" አንዱ መሆኑን ተናግሯል።


ተደራጅቶ መሥራት ትልቅ ለውጥ እንደሚያመጣ በራሳችን ሰርተን ባገኘነው ውጤት አረጋግጠናል ያለው ወጣቱ፣ውጤታማ በመሆናቸው ከአነስተኛ ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ መሸጋገራቸውን ገልጿል።


ለደረቅ እንጀራ አቅርቦት ሥራቸው የሚሆን ከ500 ሺህ ብር በላይ ወጪ የመሥሪያ ቁሳቁስ ማሟላታቸውን ተናግረዋል።


በደረቅ እንጀራ ማኅበር የታቀፉ ስድስት አባላት መሆናቸውን የገለጸው ወጣቱ፥ ማህበሩ በአሁኑ ወቅት ለዘጠኝ ተጨማሪ ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠሩን ተናግሯል።


በአሁኑ ወቅት ማህበሩ በሚዛን አማን ከተማ ለሚገኙ ሆቴሎች ደረቅ እንጀራን እያቀረበ ሲሆን በቅርቡም ለሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ለማቅረብ በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል።


ሌሎች የተደራጁ ወጣቶችም አቅማቸውን በማሳደግና ወደ ተሻለ ደረጃ በመሸጋገር ቦታውን ለተተኪዎች መልቀቅ እንዳለባቸው መክሯል።


ከጥቃቅን ወደ ታዳጊ መካከለኛ አንቀሳቃሽነት ከተሸጋገሩት ማህበራት መካከል ደግሞ "ጎዶልያስ የጨርቃ ጨርቅ ማኅበር" አንዱ ነው።


የማኅበሩ ሰብሳቢ ወጣት ጸጋዬ ሳህሉ፥ ማኅበሩ በ15 ሺህ ብር ካፒታል ሥራ መጀመሩን አስታውሶ፥ በአሁኑ ወቅት ከ2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ሀብት ማፍራቱን ተናግሯል።


ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝነት ሲሸጋገሩ ከከተማ አስተዳደሩ ባገኙት 500 ካሬ ሜትር የመሥሪያ ቦታ ላይ ሥራውን ለማስፋፋት የሚያስችል የግንባታ ሥራ መጀመራቸውንም ጠቅሷል።


የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ሥራ፣ክህሎት፣ንግድ፣ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ምትኩ ጢሞቴዎስ በበኩላቸው፥ በበጀት ዓመቱ 10 ኢንተርፕራይዞች ከአነስተኛ ወደ መካከለኛ ደረጃ ተሸጋግረዋል።


ለዚህም ከከተማ አስተዳደሩ 1 ሺህ ካሬ ሜትር የሚጠጋ የመሥሪያ ቦታ ለኢንተርፕራይዞች መተላለፉን ገልጸው፥ በተጨማሪም 25 የመስሪያ ኮንቴነሮችን እያዘጋጀን ነው ብለዋል።


በበጀት ዓመቱ ግማሽ ዓመት ለ21 አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች 6 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር ካፒታል በመመደብ ወደ ሥራ ማስገባት መቻሉንም ጠቅሰዋል።


በሥራ ዕድል ፈጠራም ከ1 ሺህ 100 ለሚበልጡ ወጣቶች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል መፈጠሩን ገልጸው፥ የክትትልና ድጋፍ ሥራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026