የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

Feb 28, 2025

IDOPRESS

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመሆናቸው ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ መሸጋገራቸውን ገለጹ።


አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ አንቀሳቃሾች መካከል በሚዛን አማን ከተማ ከሁለት ዓመት በፊት በጫኝ አውራጅ ሥራ 23 አባላትን ይዞ የተደራጀውና ወደሥራ የገባው "ጥምረት ማኅበር" አንዱ ነው።


የማህበሩ ሰብሳቢ ወጣት ፓርቲ አርዱ እንደገለጸው፥ ማህበሩ ከ1 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር በላይ በመቆጠብ በአሁኑ ወቅት ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝነት አድጓል።


የማህበሩ አባላት በራሳቸው ፍላጎት ሽግግር ያደረጉት በአራት የተለያዩ የሥራ ዘርፎች በመሰማራት መሆኑን ጠቅሶ "ፍቅር የደረቅ እንጀራ ማኅበር" አንዱ መሆኑን ተናግሯል።


ተደራጅቶ መሥራት ትልቅ ለውጥ እንደሚያመጣ በራሳችን ሰርተን ባገኘነው ውጤት አረጋግጠናል ያለው ወጣቱ፣ውጤታማ በመሆናቸው ከአነስተኛ ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ መሸጋገራቸውን ገልጿል።


ለደረቅ እንጀራ አቅርቦት ሥራቸው የሚሆን ከ500 ሺህ ብር በላይ ወጪ የመሥሪያ ቁሳቁስ ማሟላታቸውን ተናግረዋል።


በደረቅ እንጀራ ማኅበር የታቀፉ ስድስት አባላት መሆናቸውን የገለጸው ወጣቱ፥ ማህበሩ በአሁኑ ወቅት ለዘጠኝ ተጨማሪ ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠሩን ተናግሯል።


በአሁኑ ወቅት ማህበሩ በሚዛን አማን ከተማ ለሚገኙ ሆቴሎች ደረቅ እንጀራን እያቀረበ ሲሆን በቅርቡም ለሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ለማቅረብ በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል።


ሌሎች የተደራጁ ወጣቶችም አቅማቸውን በማሳደግና ወደ ተሻለ ደረጃ በመሸጋገር ቦታውን ለተተኪዎች መልቀቅ እንዳለባቸው መክሯል።


ከጥቃቅን ወደ ታዳጊ መካከለኛ አንቀሳቃሽነት ከተሸጋገሩት ማህበራት መካከል ደግሞ "ጎዶልያስ የጨርቃ ጨርቅ ማኅበር" አንዱ ነው።


የማኅበሩ ሰብሳቢ ወጣት ጸጋዬ ሳህሉ፥ ማኅበሩ በ15 ሺህ ብር ካፒታል ሥራ መጀመሩን አስታውሶ፥ በአሁኑ ወቅት ከ2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ሀብት ማፍራቱን ተናግሯል።


ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝነት ሲሸጋገሩ ከከተማ አስተዳደሩ ባገኙት 500 ካሬ ሜትር የመሥሪያ ቦታ ላይ ሥራውን ለማስፋፋት የሚያስችል የግንባታ ሥራ መጀመራቸውንም ጠቅሷል።


የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ሥራ፣ክህሎት፣ንግድ፣ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ምትኩ ጢሞቴዎስ በበኩላቸው፥ በበጀት ዓመቱ 10 ኢንተርፕራይዞች ከአነስተኛ ወደ መካከለኛ ደረጃ ተሸጋግረዋል።


ለዚህም ከከተማ አስተዳደሩ 1 ሺህ ካሬ ሜትር የሚጠጋ የመሥሪያ ቦታ ለኢንተርፕራይዞች መተላለፉን ገልጸው፥ በተጨማሪም 25 የመስሪያ ኮንቴነሮችን እያዘጋጀን ነው ብለዋል።


በበጀት ዓመቱ ግማሽ ዓመት ለ21 አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች 6 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር ካፒታል በመመደብ ወደ ሥራ ማስገባት መቻሉንም ጠቅሰዋል።


በሥራ ዕድል ፈጠራም ከ1 ሺህ 100 ለሚበልጡ ወጣቶች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል መፈጠሩን ገልጸው፥ የክትትልና ድጋፍ ሥራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው &quot;ቡኖ - ማላ&quot; ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026