የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ካፒታል ገበያን የሁሉም ለሁሉም ለማድረግ በትኩረት ይሰራል - ሀና ተኸልኩ

Jan 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 3/2017(ኢዜአ)፦ ተአማኒነት ያለው፣ ሁሉን አሳታፊ እና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን የሚፈጥር የካፒታል ገበያ ለመገንባት በትኩረት እንደሚሰራ የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሀና ተኸልኩ ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያን ትናንት በይፋ አስጀምረዋል።

በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይም የፓናል ውይይት ተካሂዷል።


በፓናሉ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሀና ተኸልኩ ከዚህ ቀደም ለበርካታ ዓመታት የካፒታል ገበያ የሚመስሉ እንቅስቃሴዎች እንደነበሩ ገልጸዋል።

ባለፉት ዓመታት ከመንግስት የፖሊሲ አቅጣጫዎች፣ ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ ሪፎርም እና ከአጠቃላይ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ማዕቀፎች በመነሳት የካፒታል ገበያ የማደራጀት ስራ ሲከናወን መቆየቱን አመልክተዋል።

በዚህም ትልቅ ትኩረት ግልጽ የሆነ የካፒታል ገበያን የሚመራና የሚቆጣጣር የህግ ማዕቀፍ ማዘጋጀት እንደነበር ጠቅሰው የካፒታል ገበያ አዋጅ ቁጥር 1248 ጸድቆ ወደ ስራ መገባቱን ተናግረዋል።


የህግ ማዕቀፉ የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ እና ገበያውን የሚያገናኙ ተቋማት እንዲተዋወቁ ማድረጉ ነው ዋና ዳይሬክተሯ የገለጹት።

አዋጁ ገበያውን ለማቀላጠፍ የሚያመቹ ተቋማት እና ቴክኖሎጂዎች እንዲፈጠሩ የሚያስችል የአሰራር ማዕቀፍ መዘርጋቱን አመልክተዋል።

በተለይም በኢንቨስትሮች መካከል በአካል ይደረግ የነበረውን የሙዓለ ሰነዶች ግብይት በቴክኖሎጂ እንዲሆን ማድረግ መቻሉን ለአብነት ጠቅሰዋል።

አዋጁን ተከትለው የወጡ መመሪያዎች ኢንቨስተሮችን ይጎዱ የነበሩ ችግሮች ለመቅረፍ እና ለውሳኔ የሚያግዛቸውን በቂ እና ጥራታቸውን የጠበቁ መረጃዎች እንዲያገኙ የሚያስችል የአሰራር ማዕቀፍ መፈጠሩን አስረድተዋል።

ባለስልጣኑ በዋናነት የኢንቨስትመንት ጥበቃ ትኩረት አድርጎ እንደሚሰራ ነው ያነሱት።

በተጨማሪም ስለ ካፒታል ገበያ ለባለድርሻ አካላት ሰፊ የግንዛቤ የመፍጠር እና የማስተማር ስራ መከናወኑን ነው የገለጹት።

እንደ ዋና ዳይሬክተሯ ገለጻ፤ የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን በቀጣይ በሙዓለ ሰነድ አቅራቢ ዋና ኢንቨስተሩ የሚታመን የካፒታል ገበያ ለመገንባት በትኩረት ይሰራል።


በካፒታል ገበያው የባለድርሻ አካላት የነቃ ተሳትፎ እንዲኖር፣ በርካታ ምርቶች እና አገልግሎቶች ለገበያው እንዲቀርቡ እና ሁሉን አሳታፊ ለማድረግ እንደሚሰራ አመልክተዋል።

ካፒታል ገበያ የሁሉም ለሁሉም ነው ያሉት ዋና ዳይሬክተሯ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች እና የግሉ ዘርፍን ጨምሮ ሁሉም ሰው እንዲሳተፍ የሚያስችሉ አሰራሮች መኖራቸውን አንስተዋል።

በአጠቃላይ የካፒታል ገበያ የኢትዮጵያን ጥቅል ኢኮኖሚ የሚደገፍ እና የዜጎችን ህይወት የሚቀይር ዘርፍ እንዲሆን በትኩረት ይሰራል ብለዋል።

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ የተለያዩ የንግድ አይነቶችን ታሳቢ በማድረግ ሶስት ልዩ ልዩ የገበያ አይነቶችን የሚያቀርብ ነው።

እነርሱም የአክሲዮን ገበያ፣ የዕዳ ሰነድ ገበያ እና የአማራጭ ገበያ ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026