
ሐረር፤ ጥር 3/2017(ኢዜአ)፡- በሐረር ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት ስራዎች የከተማዋን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ የስራ እድል እየፈጠሩ እና በኢኮኖ ተጠቃሚ እያደረጋቸው መሆኑን አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የከተማዋ ነዋሪዎች ተናገሩ።

የከተማው ነዋሪ አቶ ጣሂር ተፈራ፤ በከተማው በኮሪደር ልማት እየተከናወኑ የሚገኙ የእግረኛ መንገድ እና ሌሎች የልማት ስራዎች የከተማዋን ውበት ከመጨመር ባለፈ የትራፊክ እንቅስቃሴ እንዲሳለጥ እያገዘ መሆኑን ተናግረዋል።

ከተማዋን የሚመጥን የልማት ስራ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተከናውኗዋል፤ እነዚህም ስራዎች የከተማዋን ውበት ከመጨመር ባለፈ ህዝቡ የእረፍት ጊዜውን የሚያሳልፍበት ስፍራ እንዲያገኝ አስችሏል ሲሉ የተናገሩት ደግሞ መምህር በፍቃዱ ታደሰ ናቸው።

ወጣት በቀለ በላይ ቀደም ሲል የቆሻሻ መጣያ የነበሩ አካባቢዎች በአሁኑ ወቅት ውብና ጽዱ ሆነው መዝናኛና መናፈሻ ስፍራዎች ሆነዋል፤ ይህም እጅግ አስደስቶናል እኔና መሰሎቼ እዚህ በመምጣት ትርፍ ጊዜያችንን እናሳልፋለን ሲልም ገልጸዋል።

የኮሪደር ልማት ስራው ፍጥነትን ባማከለ መልኩ እየተከናወነና የከተማዋን ገጽታም እየለወጠ መሆኑን የተናገሩት በከተማዋ በኮሪደር ልማት በተገነቡ የመዝናኛ ስፍራዎች ፎቶ ግራፍ በማንሳት የሚተዳደሩት አቶ ተክሉ መታፈርያ ናቸው።

በከተማው የተገነቡ የኮሪደር ልማት ስራዎች ቀደም ሲል በከተማው ውስጥ የሚታየውን የትራፊክ መጨናነቅ የቀረፈ መሆኑን የጠቀሱት የከተማው መዘጋጃ ቤት ሰራተኛ የሆኑት ወይዘሮ እስከዳር ሃይሉ ናቸው።
በከተማው በኮሪደር ልማቱ በተገነባው ኑር ፕላዛ መናፈሻ ከሚዝናኑ ደንበኞች ማዘጋጃ ቤቱ ገቢ ማግኘት መጀመሩንም ጠቅሰዋል።
በክልሉ በሶስት ምዕራፍ ተከፍሎ እየተከናወነ የሚገኘው ሁለተኛው ዙር የኮሪደር ልማት ስራ ጥቅምት 22/2017 ዓ/ም የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ በተገኙበት መጀመሩ ይታወሳል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026