
ሐረር፤ ጥር 3/2017(ኢዜአ)፡- በሐረር ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት ስራዎች የከተማዋን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ የስራ እድል እየፈጠሩ እና በኢኮኖ ተጠቃሚ እያደረጋቸው መሆኑን አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የከተማዋ ነዋሪዎች ተናገሩ።

የከተማው ነዋሪ አቶ ጣሂር ተፈራ፤ በከተማው በኮሪደር ልማት እየተከናወኑ የሚገኙ የእግረኛ መንገድ እና ሌሎች የልማት ስራዎች የከተማዋን ውበት ከመጨመር ባለፈ የትራፊክ እንቅስቃሴ እንዲሳለጥ እያገዘ መሆኑን ተናግረዋል።

ከተማዋን የሚመጥን የልማት ስራ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተከናውኗዋል፤ እነዚህም ስራዎች የከተማዋን ውበት ከመጨመር ባለፈ ህዝቡ የእረፍት ጊዜውን የሚያሳልፍበት ስፍራ እንዲያገኝ አስችሏል ሲሉ የተናገሩት ደግሞ መምህር በፍቃዱ ታደሰ ናቸው።

ወጣት በቀለ በላይ ቀደም ሲል የቆሻሻ መጣያ የነበሩ አካባቢዎች በአሁኑ ወቅት ውብና ጽዱ ሆነው መዝናኛና መናፈሻ ስፍራዎች ሆነዋል፤ ይህም እጅግ አስደስቶናል እኔና መሰሎቼ እዚህ በመምጣት ትርፍ ጊዜያችንን እናሳልፋለን ሲልም ገልጸዋል።

የኮሪደር ልማት ስራው ፍጥነትን ባማከለ መልኩ እየተከናወነና የከተማዋን ገጽታም እየለወጠ መሆኑን የተናገሩት በከተማዋ በኮሪደር ልማት በተገነቡ የመዝናኛ ስፍራዎች ፎቶ ግራፍ በማንሳት የሚተዳደሩት አቶ ተክሉ መታፈርያ ናቸው።

በከተማው የተገነቡ የኮሪደር ልማት ስራዎች ቀደም ሲል በከተማው ውስጥ የሚታየውን የትራፊክ መጨናነቅ የቀረፈ መሆኑን የጠቀሱት የከተማው መዘጋጃ ቤት ሰራተኛ የሆኑት ወይዘሮ እስከዳር ሃይሉ ናቸው።
በከተማው በኮሪደር ልማቱ በተገነባው ኑር ፕላዛ መናፈሻ ከሚዝናኑ ደንበኞች ማዘጋጃ ቤቱ ገቢ ማግኘት መጀመሩንም ጠቅሰዋል።
በክልሉ በሶስት ምዕራፍ ተከፍሎ እየተከናወነ የሚገኘው ሁለተኛው ዙር የኮሪደር ልማት ስራ ጥቅምት 22/2017 ዓ/ም የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ በተገኙበት መጀመሩ ይታወሳል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026