
ሐረር፤ ጥር 3/2017(ኢዜአ)፡- በሐረር ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት ስራዎች የከተማዋን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ የስራ እድል እየፈጠሩ እና በኢኮኖ ተጠቃሚ እያደረጋቸው መሆኑን አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የከተማዋ ነዋሪዎች ተናገሩ።

የከተማው ነዋሪ አቶ ጣሂር ተፈራ፤ በከተማው በኮሪደር ልማት እየተከናወኑ የሚገኙ የእግረኛ መንገድ እና ሌሎች የልማት ስራዎች የከተማዋን ውበት ከመጨመር ባለፈ የትራፊክ እንቅስቃሴ እንዲሳለጥ እያገዘ መሆኑን ተናግረዋል።

ከተማዋን የሚመጥን የልማት ስራ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተከናውኗዋል፤ እነዚህም ስራዎች የከተማዋን ውበት ከመጨመር ባለፈ ህዝቡ የእረፍት ጊዜውን የሚያሳልፍበት ስፍራ እንዲያገኝ አስችሏል ሲሉ የተናገሩት ደግሞ መምህር በፍቃዱ ታደሰ ናቸው።

ወጣት በቀለ በላይ ቀደም ሲል የቆሻሻ መጣያ የነበሩ አካባቢዎች በአሁኑ ወቅት ውብና ጽዱ ሆነው መዝናኛና መናፈሻ ስፍራዎች ሆነዋል፤ ይህም እጅግ አስደስቶናል እኔና መሰሎቼ እዚህ በመምጣት ትርፍ ጊዜያችንን እናሳልፋለን ሲልም ገልጸዋል።

የኮሪደር ልማት ስራው ፍጥነትን ባማከለ መልኩ እየተከናወነና የከተማዋን ገጽታም እየለወጠ መሆኑን የተናገሩት በከተማዋ በኮሪደር ልማት በተገነቡ የመዝናኛ ስፍራዎች ፎቶ ግራፍ በማንሳት የሚተዳደሩት አቶ ተክሉ መታፈርያ ናቸው።

በከተማው የተገነቡ የኮሪደር ልማት ስራዎች ቀደም ሲል በከተማው ውስጥ የሚታየውን የትራፊክ መጨናነቅ የቀረፈ መሆኑን የጠቀሱት የከተማው መዘጋጃ ቤት ሰራተኛ የሆኑት ወይዘሮ እስከዳር ሃይሉ ናቸው።
በከተማው በኮሪደር ልማቱ በተገነባው ኑር ፕላዛ መናፈሻ ከሚዝናኑ ደንበኞች ማዘጋጃ ቤቱ ገቢ ማግኘት መጀመሩንም ጠቅሰዋል።
በክልሉ በሶስት ምዕራፍ ተከፍሎ እየተከናወነ የሚገኘው ሁለተኛው ዙር የኮሪደር ልማት ስራ ጥቅምት 22/2017 ዓ/ም የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ በተገኙበት መጀመሩ ይታወሳል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026