የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በሐረር ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት ስራዎች የከተማዋን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ የስራ እድል ፈጥረዋል - ነዋሪዎች

Jan 13, 2025

IDOPRESS

ሐረር፤ ጥር 3/2017(ኢዜአ)፡- በሐረር ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት ስራዎች የከተማዋን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ የስራ እድል እየፈጠሩ እና በኢኮኖ ተጠቃሚ እያደረጋቸው መሆኑን አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የከተማዋ ነዋሪዎች ተናገሩ።


የከተማው ነዋሪ አቶ ጣሂር ተፈራ፤ በከተማው በኮሪደር ልማት እየተከናወኑ የሚገኙ የእግረኛ መንገድ እና ሌሎች የልማት ስራዎች የከተማዋን ውበት ከመጨመር ባለፈ የትራፊክ እንቅስቃሴ እንዲሳለጥ እያገዘ መሆኑን ተናግረዋል።


ከተማዋን የሚመጥን የልማት ስራ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተከናውኗዋል፤ እነዚህም ስራዎች የከተማዋን ውበት ከመጨመር ባለፈ ህዝቡ የእረፍት ጊዜውን የሚያሳልፍበት ስፍራ እንዲያገኝ አስችሏል ሲሉ የተናገሩት ደግሞ መምህር በፍቃዱ ታደሰ ናቸው።


ወጣት በቀለ በላይ ቀደም ሲል የቆሻሻ መጣያ የነበሩ አካባቢዎች በአሁኑ ወቅት ውብና ጽዱ ሆነው መዝናኛና መናፈሻ ስፍራዎች ሆነዋል፤ ይህም እጅግ አስደስቶናል እኔና መሰሎቼ እዚህ በመምጣት ትርፍ ጊዜያችንን እናሳልፋለን ሲልም ገልጸዋል።


የኮሪደር ልማት ስራው ፍጥነትን ባማከለ መልኩ እየተከናወነና የከተማዋን ገጽታም እየለወጠ መሆኑን የተናገሩት በከተማዋ በኮሪደር ልማት በተገነቡ የመዝናኛ ስፍራዎች ፎቶ ግራፍ በማንሳት የሚተዳደሩት አቶ ተክሉ መታፈርያ ናቸው።


በከተማው የተገነቡ የኮሪደር ልማት ስራዎች ቀደም ሲል በከተማው ውስጥ የሚታየውን የትራፊክ መጨናነቅ የቀረፈ መሆኑን የጠቀሱት የከተማው መዘጋጃ ቤት ሰራተኛ የሆኑት ወይዘሮ እስከዳር ሃይሉ ናቸው።

በከተማው በኮሪደር ልማቱ በተገነባው ኑር ፕላዛ መናፈሻ ከሚዝናኑ ደንበኞች ማዘጋጃ ቤቱ ገቢ ማግኘት መጀመሩንም ጠቅሰዋል።

በክልሉ በሶስት ምዕራፍ ተከፍሎ እየተከናወነ የሚገኘው ሁለተኛው ዙር የኮሪደር ልማት ስራ ጥቅምት 22/2017 ዓ/ም የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ በተገኙበት መጀመሩ ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026