የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ባለፉት አምስት ወራት 617 ቢሊዮን ብር ገቢ ተሰብስቧል - የገቢዎች ሚኒስቴር

Jan 13, 2025

IDOPRESS

ጅማ፤ ጥር 3/2017(ኢዜአ)፡- ባለፉት አምስት ወራት 617 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን የገቢዎች ሚኒስትር ወይዘሮ አይናለም ንጉሴ ገለጹ።

በጅማ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው የፋይናንስ፣ የፕላንና ገቢዎች የምክክር መድረክ ዛሬ በገቢ አሰባሰብ ላይ አተኩሮ ውይይት አድርጓል።


በዚሁ ጊዜ የገቢዎች ሚኒስትሯ ወይዘሮ አይናለም ንጉሴ፤ ባለፉት አምስት ወራት ለመሰብሰብ የታቀደው 648 ቢሊዮን ብር መሆኑን ገልጸው 617 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን ተናግረዋል።

ይህም ለመሰብሰብ ከታቀደው 95 በመቶ መሆኑን ገልጸዋል።

የበጀት ዓመቱን እቅድ ለማሳካትም የገቢ ሰብሳቢ ተቋማት የደረሰኝ ማጭበርበርንና የታክስ ስወራን መከላከል ላይ በትኩረት እንዲሰሩም አሳስበዋል።

በተጨማሪም የግብር ከፋዩን ግንዛቤ ማሳደግ የሚያስችሉ ስራዎችን ማጠናከር፣ የገቢ አሰባሰብ ሂደቱን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ማገዝም ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026