
ጅማ፤ ጥር 3/2017(ኢዜአ)፡- ባለፉት አምስት ወራት 617 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን የገቢዎች ሚኒስትር ወይዘሮ አይናለም ንጉሴ ገለጹ።
በጅማ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው የፋይናንስ፣ የፕላንና ገቢዎች የምክክር መድረክ ዛሬ በገቢ አሰባሰብ ላይ አተኩሮ ውይይት አድርጓል።

በዚሁ ጊዜ የገቢዎች ሚኒስትሯ ወይዘሮ አይናለም ንጉሴ፤ ባለፉት አምስት ወራት ለመሰብሰብ የታቀደው 648 ቢሊዮን ብር መሆኑን ገልጸው 617 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን ተናግረዋል።
ይህም ለመሰብሰብ ከታቀደው 95 በመቶ መሆኑን ገልጸዋል።
የበጀት ዓመቱን እቅድ ለማሳካትም የገቢ ሰብሳቢ ተቋማት የደረሰኝ ማጭበርበርንና የታክስ ስወራን መከላከል ላይ በትኩረት እንዲሰሩም አሳስበዋል።
በተጨማሪም የግብር ከፋዩን ግንዛቤ ማሳደግ የሚያስችሉ ስራዎችን ማጠናከር፣ የገቢ አሰባሰብ ሂደቱን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ማገዝም ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ነው ያሉት።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026