
ጅማ፤ ጥር 3/2017(ኢዜአ)፡- ባለፉት አምስት ወራት 617 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን የገቢዎች ሚኒስትር ወይዘሮ አይናለም ንጉሴ ገለጹ።
በጅማ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው የፋይናንስ፣ የፕላንና ገቢዎች የምክክር መድረክ ዛሬ በገቢ አሰባሰብ ላይ አተኩሮ ውይይት አድርጓል።

በዚሁ ጊዜ የገቢዎች ሚኒስትሯ ወይዘሮ አይናለም ንጉሴ፤ ባለፉት አምስት ወራት ለመሰብሰብ የታቀደው 648 ቢሊዮን ብር መሆኑን ገልጸው 617 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን ተናግረዋል።
ይህም ለመሰብሰብ ከታቀደው 95 በመቶ መሆኑን ገልጸዋል።
የበጀት ዓመቱን እቅድ ለማሳካትም የገቢ ሰብሳቢ ተቋማት የደረሰኝ ማጭበርበርንና የታክስ ስወራን መከላከል ላይ በትኩረት እንዲሰሩም አሳስበዋል።
በተጨማሪም የግብር ከፋዩን ግንዛቤ ማሳደግ የሚያስችሉ ስራዎችን ማጠናከር፣ የገቢ አሰባሰብ ሂደቱን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ማገዝም ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ነው ያሉት።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026