የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ለግሉ ዘርፍ የተሰጠውን ትኩረት በመጠቀም የመኖሪያ ቤት ችግሮችን ለመፍታት በትኩረት እየሰራን ነው- አቶ ዮናስ ታደሰ

Jan 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2017(ኢዜአ)፦መንግሥት ለግሉ ዘርፍ የሰጠውን ትኩረት በመጠቀም የመኖሪያ ቤት ችግሮችን ለመፍታት ትኩረት መደረጉን የኦቪድ ሆልዲንግ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዮናስ ታደሰ ገለጹ።

የኦቪድ ሆልዲንግ እንደ አውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር እስከ 2030 ለማሳካት ያለመውን የአምስት ዓመት ሥትራቴጂክ ዕቅድ ዛሬ ይፋ አድርጓል።

የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ እቅዱም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት፣ አጋርነትና ትብብር፣ ቴክኖሎጂና ፈጠራ እንዲሁም ብቃትና ለደንበኞች ትኩረት መስጠት የሚሉ መርሆዎችን የያዘ ነው።


ዋና ሥራ አስፈፃሚው በመርሃ-ግብሩ ላይ በሰጡት ማብራሪያ ለደንበኞቻችን የገባነውን ቃል ኪዳን እና ለተሻለች ኢትዮጵያ እውን መሆን በቁርጠኝነት እንሰራለን ብለዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያን በይፋ ባስጀመሩበት ማግስት ስትራቴጂው ይፋ መደረጉም መልካም አጋጣሚ መሆኑን አንስተዋል፡፡

በኢትዮጵያ በመንግሥት አነሳሽነት የተጀመረው የቤት ልማት አጋርነት ለግሉ ዘርፍ ተሳትፎ ቁልፍ ሚና እንዳለውም ገልጸዋል።

በመሆኑም የግሉ ዘርፍ መንግሥት የሰጠውን ትኩረት በመጠቀም ለኢትዮጵያ እድገትና ብልጽግና ቁልፍ ሚናውን ሊጫወት ይገባል ብለዋል።

መንግሥት ለግሉ ዘርፍ የሰጠውን ትኩረት በመጠቀም የመኖሪያ ቤት ችግሮችን ለመፍታት በትኩረት እየሰራን ነው ያሉት ዋና ሥራ አስፈፃሚው፤ በኢትዮጵያ ለዘመናት የቆየው የቤት አቅርቦት ችግሮች በጥናት መለየታቸውን ገልጸዋል።

በመሆኑም በዘርፉ ላይ የታዩትን ሳንካዎች እንደ ችግር ከማየት ይልቅ ወደ መልካም አጋጣሚነት ለመቀየር ቆርጠን ተነስተናል ብለዋል።

በዚህም የኦቪድ ሆልዲንግ 2030 ስትራቴጂ እውን ለማድረግ በመሰረታዊ ችግሮች ላይ የሚወሰዱ የመፍትሔ ርምጃዎች ላይ አተኩረን እንሰራለን ነው ያሉት፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025