የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ለግሉ ዘርፍ የተሰጠውን ትኩረት በመጠቀም የመኖሪያ ቤት ችግሮችን ለመፍታት በትኩረት እየሰራን ነው- አቶ ዮናስ ታደሰ

Jan 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2017(ኢዜአ)፦መንግሥት ለግሉ ዘርፍ የሰጠውን ትኩረት በመጠቀም የመኖሪያ ቤት ችግሮችን ለመፍታት ትኩረት መደረጉን የኦቪድ ሆልዲንግ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዮናስ ታደሰ ገለጹ።

የኦቪድ ሆልዲንግ እንደ አውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር እስከ 2030 ለማሳካት ያለመውን የአምስት ዓመት ሥትራቴጂክ ዕቅድ ዛሬ ይፋ አድርጓል።

የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ እቅዱም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት፣ አጋርነትና ትብብር፣ ቴክኖሎጂና ፈጠራ እንዲሁም ብቃትና ለደንበኞች ትኩረት መስጠት የሚሉ መርሆዎችን የያዘ ነው።


ዋና ሥራ አስፈፃሚው በመርሃ-ግብሩ ላይ በሰጡት ማብራሪያ ለደንበኞቻችን የገባነውን ቃል ኪዳን እና ለተሻለች ኢትዮጵያ እውን መሆን በቁርጠኝነት እንሰራለን ብለዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያን በይፋ ባስጀመሩበት ማግስት ስትራቴጂው ይፋ መደረጉም መልካም አጋጣሚ መሆኑን አንስተዋል፡፡

በኢትዮጵያ በመንግሥት አነሳሽነት የተጀመረው የቤት ልማት አጋርነት ለግሉ ዘርፍ ተሳትፎ ቁልፍ ሚና እንዳለውም ገልጸዋል።

በመሆኑም የግሉ ዘርፍ መንግሥት የሰጠውን ትኩረት በመጠቀም ለኢትዮጵያ እድገትና ብልጽግና ቁልፍ ሚናውን ሊጫወት ይገባል ብለዋል።

መንግሥት ለግሉ ዘርፍ የሰጠውን ትኩረት በመጠቀም የመኖሪያ ቤት ችግሮችን ለመፍታት በትኩረት እየሰራን ነው ያሉት ዋና ሥራ አስፈፃሚው፤ በኢትዮጵያ ለዘመናት የቆየው የቤት አቅርቦት ችግሮች በጥናት መለየታቸውን ገልጸዋል።

በመሆኑም በዘርፉ ላይ የታዩትን ሳንካዎች እንደ ችግር ከማየት ይልቅ ወደ መልካም አጋጣሚነት ለመቀየር ቆርጠን ተነስተናል ብለዋል።

በዚህም የኦቪድ ሆልዲንግ 2030 ስትራቴጂ እውን ለማድረግ በመሰረታዊ ችግሮች ላይ የሚወሰዱ የመፍትሔ ርምጃዎች ላይ አተኩረን እንሰራለን ነው ያሉት፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026