
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2017(ኢዜአ)፦መንግሥት ለግሉ ዘርፍ የሰጠውን ትኩረት በመጠቀም የመኖሪያ ቤት ችግሮችን ለመፍታት ትኩረት መደረጉን የኦቪድ ሆልዲንግ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዮናስ ታደሰ ገለጹ።
የኦቪድ ሆልዲንግ እንደ አውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር እስከ 2030 ለማሳካት ያለመውን የአምስት ዓመት ሥትራቴጂክ ዕቅድ ዛሬ ይፋ አድርጓል።
የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ እቅዱም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት፣ አጋርነትና ትብብር፣ ቴክኖሎጂና ፈጠራ እንዲሁም ብቃትና ለደንበኞች ትኩረት መስጠት የሚሉ መርሆዎችን የያዘ ነው።

ዋና ሥራ አስፈፃሚው በመርሃ-ግብሩ ላይ በሰጡት ማብራሪያ ለደንበኞቻችን የገባነውን ቃል ኪዳን እና ለተሻለች ኢትዮጵያ እውን መሆን በቁርጠኝነት እንሰራለን ብለዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያን በይፋ ባስጀመሩበት ማግስት ስትራቴጂው ይፋ መደረጉም መልካም አጋጣሚ መሆኑን አንስተዋል፡፡
በኢትዮጵያ በመንግሥት አነሳሽነት የተጀመረው የቤት ልማት አጋርነት ለግሉ ዘርፍ ተሳትፎ ቁልፍ ሚና እንዳለውም ገልጸዋል።
በመሆኑም የግሉ ዘርፍ መንግሥት የሰጠውን ትኩረት በመጠቀም ለኢትዮጵያ እድገትና ብልጽግና ቁልፍ ሚናውን ሊጫወት ይገባል ብለዋል።
መንግሥት ለግሉ ዘርፍ የሰጠውን ትኩረት በመጠቀም የመኖሪያ ቤት ችግሮችን ለመፍታት በትኩረት እየሰራን ነው ያሉት ዋና ሥራ አስፈፃሚው፤ በኢትዮጵያ ለዘመናት የቆየው የቤት አቅርቦት ችግሮች በጥናት መለየታቸውን ገልጸዋል።
በመሆኑም በዘርፉ ላይ የታዩትን ሳንካዎች እንደ ችግር ከማየት ይልቅ ወደ መልካም አጋጣሚነት ለመቀየር ቆርጠን ተነስተናል ብለዋል።
በዚህም የኦቪድ ሆልዲንግ 2030 ስትራቴጂ እውን ለማድረግ በመሰረታዊ ችግሮች ላይ የሚወሰዱ የመፍትሔ ርምጃዎች ላይ አተኩረን እንሰራለን ነው ያሉት፡፡
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026