
አዲስ አበባ፤ጥር 5/2017(ኢዜአ)፡-የሳዑዲ ጎልድ ሪፋይነሪ ኩባንያ (Saudi Gold Refinery Co) በኢትዮጵያ በማዕድን ዘርፍ የኢንቨስትመንት ስራ ለመጀመር የሚያስችል እንቅስቃሴ መጀመሩን አስታወቀ።
በሳዑዲ አረቢያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሙክታር ከድር (ዶ/ር) ከኩባንያው ባለቤት ሱሌይማን ሳሌህ አሎታይም ጋር በሪያድ ተወያይተዋል።
ውይይቱ ኩባንያው በኢትዮጵያ ማዕድን ዘርፍ ኢንቨስት ማድረግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው።
አምባሳደር ሙክታር፥ ኢትዮጵያ ከፍተኛ የማዕድን ክምችት ያላት ሃገር መሆኗንና መንግስት በዘርፉ የተለያዩ ማበረታቻዎችን ጨምሮ ምቹ የኢንቨስትመንት ምህዳር ለመፍጠር የሚያስችሉ የፖሊሲ ማሻሻያዎችን እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
በተጨማሪም ኩባንያው በዘርፉ ያለውን ልምድ እና ቴክኖሎጂ በመጠቀም በኢትዮጵያ ኢንቨስት እንዲያደርግ ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን፣ኤምባሲውም አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አመልክተዋል።
የሳዑዲ ጎልድ ሪፋይነሪ ኩባንያ (Saudi Gold Refinery Co) ሱሌይማን ሳሌህ አሎታይም ኩባንያቸው በኢትዮጵያ ኢንቨስት ለማድረግ ከፍተኛ ፍላጎት እንዳለው አመልክተዋል።
ኩባንያው በማዕድን ዘርፍ ስራውን ለማስጀመር የሚያስችል እንቅስቃሴ እንደጀመረ መግለጻቸውን በሪያድ ከኢትዮጵያ ኤምባሲ የተገኘ መረጃ ያመለክታል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026