የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>የሳዑዲ ጎልድ ሪፋይነሪ ኩባንያ በኢትዮጵያ በማዕድን ዘርፍ ኢንቨስትመንት ለመሰማራት እንቅስቃሴ ጀመረ</p>

Jan 14, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ጥር 5/2017(ኢዜአ)፡-የሳዑዲ ጎልድ ሪፋይነሪ ኩባንያ (Saudi Gold Refinery Co) በኢትዮጵያ በማዕድን ዘርፍ የኢንቨስትመንት ስራ ለመጀመር የሚያስችል እንቅስቃሴ መጀመሩን አስታወቀ።

በሳዑዲ አረቢያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሙክታር ከድር (ዶ/ር) ከኩባንያው ባለቤት ሱሌይማን ሳሌህ አሎታይም ጋር በሪያድ ተወያይተዋል።

ውይይቱ ኩባንያው በኢትዮጵያ ማዕድን ዘርፍ ኢንቨስት ማድረግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው።

አምባሳደር ሙክታር፥ ኢትዮጵያ ከፍተኛ የማዕድን ክምችት ያላት ሃገር መሆኗንና መንግስት በዘርፉ የተለያዩ ማበረታቻዎችን ጨምሮ ምቹ የኢንቨስትመንት ምህዳር ለመፍጠር የሚያስችሉ የፖሊሲ ማሻሻያዎችን እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

በተጨማሪም ኩባንያው በዘርፉ ያለውን ልምድ እና ቴክኖሎጂ በመጠቀም በኢትዮጵያ ኢንቨስት እንዲያደርግ ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን፣ኤምባሲውም አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አመልክተዋል።

የሳዑዲ ጎልድ ሪፋይነሪ ኩባንያ (Saudi Gold Refinery Co) ሱሌይማን ሳሌህ አሎታይም ኩባንያቸው በኢትዮጵያ ኢንቨስት ለማድረግ ከፍተኛ ፍላጎት እንዳለው አመልክተዋል።

ኩባንያው በማዕድን ዘርፍ ስራውን ለማስጀመር የሚያስችል እንቅስቃሴ እንደጀመረ መግለጻቸውን በሪያድ ከኢትዮጵያ ኤምባሲ የተገኘ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026