የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ትረስት ፈንድ የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ አስር ፕሮጀክቶችን እያከናወነ ነው</p>

Jan 14, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ጥር 6 /2017 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ትረስት ፈንድ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ አስር ፕሮጀክቶችን እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ፡፡

የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ትረስት ፈንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ2010 ዓ.ም በአሜሪካ ካደረጉት ጉብኝት በኋላ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ለሀገራቸው በቀን ከሚጠጡት ማኪያቶ ላይ ቀንሰው አንድ ዶላር እንዲያዋጡ ያስተላለፉትን ጥሪ ተከትሎ የተመሰረተ ተቋም ነው።


ትረስት ፈንዱ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ለኮቪድ-19 ምላሽና ለንፅህና አገልግሎት አቅርቦት 2 ነጥብ 9 ሚሊየን ዶላር እንዲሁም ለአስቸኳይ ጊዜ ምላሽ 1 ነጥብ 72 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ማድረጉ ተጠቁሟል፡፡

በኢትዮጵያ ዳያስፖራ ትረስት ፈንድ የስትራቴጂ አማካሪ አብርሃም አስራት ለኢዜአ እንዳሉት፤ ትረስት ፈንዱ 14 የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች፣የንፅህና አገልግሎት መስጫ ግንባታ፣ 48 ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ የስነ-ምግብና ሌሎች ፕሮጀክቶችን ማከናወኑን ተናግረዋል፡፡

ትረስት ፈንዱ ባለፉት አመታት በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉ ስራዎችን ሲያከናውን መቆየቱን አስታውሰዋል።

በእነኚህም የልማት ፕሮጀክቶች ከ57 ሺህ በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ ያደረገ መሆኑን ጠቁመው በአሁኑ ጊዜም በ1 ነጥብ 21 ሚሊየን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ አስር ፕሮጀክቶችን እያከናወነ መሆኑን አስታውቀዋል።

ፕሮጀክቶችም የህክምና ተቋማትን ለማገዝ፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ የልማት ፕሮጀክቶችን ለመደገፍ፣የአስቸኳይ ጊዜ እርዳታዎችን በመለየት ድጋፍ የሚሰጡ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በቀጣይ የዳያስፖራውን አቅም በማሰባሰብ በሀገሪቱ ያሉ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ለመፍታት እንደሚሰራም ነው ያስረዱት።

በሌላ በኩል ስታርት አፖችና ፈጠራን ለማበረታታት የግሬት ሬፍት ቫሊ ኢኖቬሽን ጉባኤ ላይም በግብርና፣ ጤናና በትምህርት ዘርፍ አዳዲስ የፈጠራ ውጤቶችን ይዘው ለሚቀርቡ ወጣቶች ሽልማት መዘጋጀቱን ገልፀዋል።

ውድድሩ ሁሉንም ኢትዮጵያዊያን ያሳተፈ እንደነበር አንስተው የላቀ የፈጠራ ውጤቶችን ይዘው ለሚቀርቡ አሸናፊዎች የ750 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ሽልማት መዘጋጀቱንም አስረድተዋል።

ጉባኤው ከጥር 23 እስከ ጥር 24 ቀን 2017 ዓ.ም የሚካሄድ ሲሆን የፓናል ውይይቶች፣ ወርክሾፖችና ከኢንዱስትሪ ጋር የትውውቅ መድረክን ያካተተ ነው ብለዋል።

የጉባኤው ዓላማ ወጣቶች ለማህበረሰቡ ችግሮች መፍትሄ የሚሆኑ ሃሳብን እንዲያመነጩ በማበረታታት የፈጠራ ባህልን ማስፋት መሆኑንም ነው የጠቆሙት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026