የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>ወንጂ ሸዋ ስኳር ፋብሪካ የአዋጭነት ጥናት ሰነድ ተረከበ</p>

Jan 15, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2017(ኢዜአ)፦ የኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶች አገልግሎት የወንጂ ሸዋ ስኳር ፋብሪካ የአዋጭነት ጥናት ሠነድን አጠናቆ አስረክቧል።

ለኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ተጠሪ ተቋም የሆነው የኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶች አገልግሎት በጥናትና ማማከር ዘርፍ፤ በአዋጭነት ጥናት፤ በንብረት ትመና እና በተለያዩ የአገልገሎት ዘርፎች ከተለያዩ መንግስት ተቋማት ጋር ላለፉት ዓመታት ሲሰራ የቆየ አንጋፋ ተቋም ነው።

በዚህንም አገልግሎቱ በወንጂ ሸዋ ስኳር ፋብሪካ ላይ ያደረገውን የአዋጭነት ጥናት አጠናቆ ዛሬ አስረክቧል።

የኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶች አገልግሎት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሽፈራው ሰለሞን እና የወንጂ ሸዋ ስኳር ፋብሪካ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ጀማል አማን የጥናት ሰነዱን ተረካክበዋል።

አቶ ሽፈራው በዚሁ ወቅት እንደገለፁት የአዋጭነት ጥናት ሰነድ ፋብሪካውን በፍጥነት ወደ ተግባር ገብቶ የሃገር ውስጥ የስኳር ተደራሽነት ሽፋን ከማሳደጉ በተጨማሪ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪነት ያግዛል።

የወንጅ ሸዋ ስኳር ፋብሪካ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ጀማል አማን በበኩላቸው ወንጅ ሸዋ ስኳር ፋብሪካ እንደ ሃገር በርካታ ስራዎችን የሚሰራ ፋብሪካ መሆኑን ጠቅሰዋል።

አሁን የተረከበው የአዋጭነት ጥናት ሰነድን በአጭር ጊዜ ወደ ትግበራ እንደሚገባ ማረጋገጣቸውን ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ያገነኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026