
አዲስ አበባ፤ ጥር 9/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮ ቴሌኮም የዲጂታል አገልግሎት ተጠቃሚነት ክፍተትን ለማጥበብ፣ ኢኮኖሚያዊ ዕድሎችን ለመፍጠር እየተጋ እንደሚገኝ የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ ገልጸዋል።
ዋና ስራ አስፈጻሚዋ በአፍሪካ ልማት ባንክ ምክትል ፕሬዚዳንት ሰለሞን ኩዋይኖርና የባንኩ የምስራቅ አፍሪካ ሪጅን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሊያንድር ባሶሌ(ዶ/ር) ከተመራ ከፍተኛ ልዑክ ጋር በአፍሪካ የዲጂታል መጻኢ እድገት ዙሪያ ተወያይተዋል።
በውይይቱ ላይም ዋና ስራ አስፈጻሚዋ ኢትዮ ቴሌኮም ከአፍሪካ ግዙፉ የቴሌኮም ኦፕሬተር እንደመሆኑ የዲጂታል አገልግሎት ተጠቃሚነት ክፍተትን ለማጥበብ፣ ኢኮኖሚያዊ ዕድሎችን ለመፍጠር፣ አካታችና ቀጣይነት ያለው እድገትን ለማምጣት እየተጋ እንደሚገኝ አብራርተዋል።

አክለውም አፍሪካ ያሉባትን ተግዳሮቶች ለማለፍ፣ አዳዲስ ዕድሎችንና ዘላቂ ልማትን ለመፍጠር ቴክኖሎጂን እና ዲጂታል መፍትሔዎችን መጠቀም እንዳለባትም አጽንኦት ሰጥተዋል።
ይህ ዘርፈ ብዙ ጥረት የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞን ከማሳካት ባለፈ የአፍሪካ ዲጂታል አቅምን ለማጎልበት ትልቅ አስተዋፅኦ ያለው በመሆኑ የቴሌኮም ኢንዱስትሪውን በፋይናንስ መደገፍ ከትስስር ባሻገር አጠቃላይ የአህጉሪቱን ኢኮኖሚ ለማጎልበት ከፍተኛ ሚና እንዳለው አጽንኦት ሰጥተዋል።
ኢትዮ ቴሌኮም የሀገራችንን ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ራዕይ ከግብ ለማድረስ የተለያዩ ፋይናንሰሮችን ጨምሮ ቁልፍ ዓለም አቀፍ አጋሮችን በመሳብ የበለጸገች ዲጂታል አፍሪካን ራዕይ እውን የማድረግ ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
የባንኩ ምክትል ፕሬዚዳንት ሰለሞን ኩዋይኖር የኢትዮ ቴሌኮምን ፈጣን ዕድገትና ለኢትዮጵያ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ እየተጫወተ ስለሚገኘው አስተዋፅኦ ያላቸውን አድናቆት ገልጸዋል።
ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በአጋርነት ሊሰሩባቸው የሚችሉባቸውን ጉዳዮች በማብራራት የአፍሪካ ልማት ባንክ የኩባንያውን ዲጂታል ኢኒሸቲቭ ለመደገፍ ያለውን ዝግጁነት አረጋግጠዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026