
አዲስ አበባ፤ ጥር 9/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮ ቴሌኮም የዲጂታል አገልግሎት ተጠቃሚነት ክፍተትን ለማጥበብ፣ ኢኮኖሚያዊ ዕድሎችን ለመፍጠር እየተጋ እንደሚገኝ የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ ገልጸዋል።
ዋና ስራ አስፈጻሚዋ በአፍሪካ ልማት ባንክ ምክትል ፕሬዚዳንት ሰለሞን ኩዋይኖርና የባንኩ የምስራቅ አፍሪካ ሪጅን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሊያንድር ባሶሌ(ዶ/ር) ከተመራ ከፍተኛ ልዑክ ጋር በአፍሪካ የዲጂታል መጻኢ እድገት ዙሪያ ተወያይተዋል።
በውይይቱ ላይም ዋና ስራ አስፈጻሚዋ ኢትዮ ቴሌኮም ከአፍሪካ ግዙፉ የቴሌኮም ኦፕሬተር እንደመሆኑ የዲጂታል አገልግሎት ተጠቃሚነት ክፍተትን ለማጥበብ፣ ኢኮኖሚያዊ ዕድሎችን ለመፍጠር፣ አካታችና ቀጣይነት ያለው እድገትን ለማምጣት እየተጋ እንደሚገኝ አብራርተዋል።

አክለውም አፍሪካ ያሉባትን ተግዳሮቶች ለማለፍ፣ አዳዲስ ዕድሎችንና ዘላቂ ልማትን ለመፍጠር ቴክኖሎጂን እና ዲጂታል መፍትሔዎችን መጠቀም እንዳለባትም አጽንኦት ሰጥተዋል።
ይህ ዘርፈ ብዙ ጥረት የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞን ከማሳካት ባለፈ የአፍሪካ ዲጂታል አቅምን ለማጎልበት ትልቅ አስተዋፅኦ ያለው በመሆኑ የቴሌኮም ኢንዱስትሪውን በፋይናንስ መደገፍ ከትስስር ባሻገር አጠቃላይ የአህጉሪቱን ኢኮኖሚ ለማጎልበት ከፍተኛ ሚና እንዳለው አጽንኦት ሰጥተዋል።
ኢትዮ ቴሌኮም የሀገራችንን ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ራዕይ ከግብ ለማድረስ የተለያዩ ፋይናንሰሮችን ጨምሮ ቁልፍ ዓለም አቀፍ አጋሮችን በመሳብ የበለጸገች ዲጂታል አፍሪካን ራዕይ እውን የማድረግ ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
የባንኩ ምክትል ፕሬዚዳንት ሰለሞን ኩዋይኖር የኢትዮ ቴሌኮምን ፈጣን ዕድገትና ለኢትዮጵያ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ እየተጫወተ ስለሚገኘው አስተዋፅኦ ያላቸውን አድናቆት ገልጸዋል።
ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በአጋርነት ሊሰሩባቸው የሚችሉባቸውን ጉዳዮች በማብራራት የአፍሪካ ልማት ባንክ የኩባንያውን ዲጂታል ኢኒሸቲቭ ለመደገፍ ያለውን ዝግጁነት አረጋግጠዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026