የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>የሚገነቡ ህንጻዎች ዘመኑን የዋጁና ዘላቂ እንዲሆኑ ኮዶችንና ስታንዳርዶችን የማሻሻል ሥራዎች እየተሰሩ ነው - የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር</p>

Jan 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 9/2017(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የሚገነቡ ህንጻዎች ዘመኑን የዋጁና ዘላቂ እንዲሆኑ የህንጻ ኮዶችንና ስታንዳርዶችን የማሻሻል ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ገለጹ።

የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለሥልጣን ከከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴርና ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የምክክር መድረክ ዛሬ ተካሂዷል።


በመድረኩ ላይ የህንጻ ኮዶችና ስታንዳርዶች እንዲሁም የሥራ ላይ ደህንነት እና ጤንነት ላይ ትኩረት ያደረጉ ጹሁፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።

የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ዘርፉ በሥራ ዕድል ፈጠራና በኢኮኖሚ እድገቱ ውስጥ የሚጫወተውን ሚና ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ አዳዲስ አሰራሮችን ከመተግበር ባለፈ ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂዎች እንዲጠቀም ማድረግ ይገባል።

ለዚህም እያደገ ከመጣው የመሰረተ ልማት ፍላጎትና አቅርቦት ጋር የሚጣጣም የህንጻ ኮድና ስታንዳርዶችን ሥራ ላይ ማዋል ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፤ ይህም ችግሩን የሚቋቋም ዘላቂ ግንባታዎች እንዲኖሩ የሚያስችል ነው ብለዋል።

ለዚህም ሚኒስቴሩ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ከ2007 ዓ.ም ጀምሮ ሥራ ላይ የዋለውን የኢትዮጵያ የህንጻ ኮድና ስታንዳርዶች ማሻሻል የሚያስችል ጥናት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

ኮድና ስታንዳርድ መሻሻሉ ከግንባታ ግብዓት፣ ቴክኖሎጂ እና ዘርፉ ከሚፈልገው ክህሎት አኳያ ዘመኑን የዋጁ አሰራሮችን ለመከተል ጉልህ ፋይዳ እንዳለው አብራርተዋል።

የሥራ ላይ ደህንነት እና ጤንነትን በተመለከተ ሕጎችና ደንቦችን ተግባር ላይ ማዋል የሚያስችል የህንጻ አዋጅ መውጣቱንም ገልጸዋል።

የግንባታ ሰራተኞች የሥራ ላይ ደህንነትና ጤንነትን በተመለከተም ሚኒስቴሩ ከባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ጥናቶችን በማካሄድ የምክረ ሀሳቦች ሰነዶች መዘጋጀታቸውን ጠቁመው፤ በጥንቃቄ ጉድለት ሳቢያ በሰራተኞች ላይ የሚደርስን ጉዳት ለመቀነስ፣ አደጋ ሲያጋጥም ተጎጂዎች ፈጣን ህክምና የሚያገኙበት ሥርዓትን ያካተተ መሆኑም ተናግረዋል።

ሚኒስትሯ አክለውም የግንባታ ደህንነትና ጤንነት መረጃ ማሰባሰቢያ ሶፍትዌር መልማቱን ጠቁመዋል።

በአሁኑ ወቅት እየተከሰተ ያለው የርዕደ መሬት ጉዳይ ታሳቢ ያደረጉ ሥራዎች በቀጣይ የሚከናወኑ መሆኑን ገልጸው፤ ለዚህም ሚኒስቴሩ ከባለድርሻ አካላት ባለሙያዎች የሚቀርቡ ምክረ ሀሳቦችን በመቀበል ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጁ መሆኑንም አረጋግጠዋል።


የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር መስፍን ነገዎ(ኢ/ር) በበኩላቸው ከዚህ ቀደም 17 የሕንጻ ኮዶች ስራ ላይ እንደነበሩ አስታውሰው፤ አሁን ላይ የተሻሻሉ አሰራሮችን የያዙ ኮዶችን ወደ 30 ከፍ ማድረግ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑም ጠቁመዋል።

ህንጻዎች የተሟላ የስልክ ኔት ወርክ እንዲኖራቸው የሚያስችሉ ቴክኖሎጂዎችን እንዲጠቀሙ የሚያደርግ አስገዳጅ አሰራር እንደሚዘረጋም አብራርተዋል።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህርና የኮንስትራክሽን ባለሙያ ኢሳያስ ገብረዮሃንስ (ዶ/ር) ኮዶችና ስታንዳርዶች በኢትዮጵያ በአመዛኙ ከአውሮፓ የተቀዱ መሆናቸውን አስታውሰው ማሻሻያው ኮዶችና ስታንዳርዶቹ ከኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ ጋር የተጣጣሙ እንዲሆኑ ለማድረግ ያለመ ነው ብለዋል።


ረጅም ጊዜ ያስቆጠሩ ህንጻዎች አደጋዎችን መቋቋም እንዲችሉ እንዴት መጠናከር አለባቸው የሚለውም በማሻሻያው መካተቱን ጠቁመው የርዕደ መሬት ተጋላጭነት እና የሚወሰዱ የጥንቃቄ እርምጃዎችን ታሳቢ ተደርገው እየተሰሩ መሆኑንም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው &quot;ቡኖ - ማላ&quot; ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026