የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>የሚገነቡ ህንጻዎች ዘመኑን የዋጁና ዘላቂ እንዲሆኑ ኮዶችንና ስታንዳርዶችን የማሻሻል ሥራዎች እየተሰሩ ነው - የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር</p>

Jan 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 9/2017(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የሚገነቡ ህንጻዎች ዘመኑን የዋጁና ዘላቂ እንዲሆኑ የህንጻ ኮዶችንና ስታንዳርዶችን የማሻሻል ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ገለጹ።

የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለሥልጣን ከከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴርና ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የምክክር መድረክ ዛሬ ተካሂዷል።


በመድረኩ ላይ የህንጻ ኮዶችና ስታንዳርዶች እንዲሁም የሥራ ላይ ደህንነት እና ጤንነት ላይ ትኩረት ያደረጉ ጹሁፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።

የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ዘርፉ በሥራ ዕድል ፈጠራና በኢኮኖሚ እድገቱ ውስጥ የሚጫወተውን ሚና ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ አዳዲስ አሰራሮችን ከመተግበር ባለፈ ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂዎች እንዲጠቀም ማድረግ ይገባል።

ለዚህም እያደገ ከመጣው የመሰረተ ልማት ፍላጎትና አቅርቦት ጋር የሚጣጣም የህንጻ ኮድና ስታንዳርዶችን ሥራ ላይ ማዋል ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፤ ይህም ችግሩን የሚቋቋም ዘላቂ ግንባታዎች እንዲኖሩ የሚያስችል ነው ብለዋል።

ለዚህም ሚኒስቴሩ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ከ2007 ዓ.ም ጀምሮ ሥራ ላይ የዋለውን የኢትዮጵያ የህንጻ ኮድና ስታንዳርዶች ማሻሻል የሚያስችል ጥናት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

ኮድና ስታንዳርድ መሻሻሉ ከግንባታ ግብዓት፣ ቴክኖሎጂ እና ዘርፉ ከሚፈልገው ክህሎት አኳያ ዘመኑን የዋጁ አሰራሮችን ለመከተል ጉልህ ፋይዳ እንዳለው አብራርተዋል።

የሥራ ላይ ደህንነት እና ጤንነትን በተመለከተ ሕጎችና ደንቦችን ተግባር ላይ ማዋል የሚያስችል የህንጻ አዋጅ መውጣቱንም ገልጸዋል።

የግንባታ ሰራተኞች የሥራ ላይ ደህንነትና ጤንነትን በተመለከተም ሚኒስቴሩ ከባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ጥናቶችን በማካሄድ የምክረ ሀሳቦች ሰነዶች መዘጋጀታቸውን ጠቁመው፤ በጥንቃቄ ጉድለት ሳቢያ በሰራተኞች ላይ የሚደርስን ጉዳት ለመቀነስ፣ አደጋ ሲያጋጥም ተጎጂዎች ፈጣን ህክምና የሚያገኙበት ሥርዓትን ያካተተ መሆኑም ተናግረዋል።

ሚኒስትሯ አክለውም የግንባታ ደህንነትና ጤንነት መረጃ ማሰባሰቢያ ሶፍትዌር መልማቱን ጠቁመዋል።

በአሁኑ ወቅት እየተከሰተ ያለው የርዕደ መሬት ጉዳይ ታሳቢ ያደረጉ ሥራዎች በቀጣይ የሚከናወኑ መሆኑን ገልጸው፤ ለዚህም ሚኒስቴሩ ከባለድርሻ አካላት ባለሙያዎች የሚቀርቡ ምክረ ሀሳቦችን በመቀበል ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጁ መሆኑንም አረጋግጠዋል።


የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር መስፍን ነገዎ(ኢ/ር) በበኩላቸው ከዚህ ቀደም 17 የሕንጻ ኮዶች ስራ ላይ እንደነበሩ አስታውሰው፤ አሁን ላይ የተሻሻሉ አሰራሮችን የያዙ ኮዶችን ወደ 30 ከፍ ማድረግ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑም ጠቁመዋል።

ህንጻዎች የተሟላ የስልክ ኔት ወርክ እንዲኖራቸው የሚያስችሉ ቴክኖሎጂዎችን እንዲጠቀሙ የሚያደርግ አስገዳጅ አሰራር እንደሚዘረጋም አብራርተዋል።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህርና የኮንስትራክሽን ባለሙያ ኢሳያስ ገብረዮሃንስ (ዶ/ር) ኮዶችና ስታንዳርዶች በኢትዮጵያ በአመዛኙ ከአውሮፓ የተቀዱ መሆናቸውን አስታውሰው ማሻሻያው ኮዶችና ስታንዳርዶቹ ከኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ ጋር የተጣጣሙ እንዲሆኑ ለማድረግ ያለመ ነው ብለዋል።


ረጅም ጊዜ ያስቆጠሩ ህንጻዎች አደጋዎችን መቋቋም እንዲችሉ እንዴት መጠናከር አለባቸው የሚለውም በማሻሻያው መካተቱን ጠቁመው የርዕደ መሬት ተጋላጭነት እና የሚወሰዱ የጥንቃቄ እርምጃዎችን ታሳቢ ተደርገው እየተሰሩ መሆኑንም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026