
አዲስ አበባ፤ ጥር 9/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ቻይና ተጨማሪ መስኮችን በመለየት ጠንካራ የንግድ ትስስራቸውን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር እንደሚሰሩ አስታወቁ።
የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) በቻይና መንግስት ምክር ቤት የልማት ምርምር ማዕከል ፕሬዝዳንት ሉ ሃኦ ከተመራ ልዑክ ጋር ዛሬ ተወያይተዋል።
ሚኒስትሩ ከልዑኩ ጋር በኢትዮጵያና ቻይና የንግድ ግንኙነት ዙሪያ ሰፊ ውይይት ማድረጋቸውን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል።
በውይይቱ ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን ጠንካራ የንግድ ግንኙነት ወደ ላቀ ትብብር ማሸጋገር የሚያስችሉ መስኮች መለየታቸውን አመልክተዋል።
በተለይም ኢትዮጵያ ወደ ቻይና የምትልካቸውን ምርቶች ማሳደግና የሁለቱን ሀገራት ኢኮኖሚ ተጠቃሚ የሚያደርጉ ተጨማሪ መስኮችን የዳሰሰ ውጤታማ ውይይት መደረጉን ጠቁመዋል።
ልዑኩ የጥራት መንደርን መጎበኘቱንና ኢትዮጵያ ለጥራት ያላትን ቁርጠኝነት ማሳየት እንደተቻለም ነው ሚኒስትሩ የገለጹት።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026