አዲስ አበባ፤ ጥር 9/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ቻይና ተጨማሪ መስኮችን በመለየት ጠንካራ የንግድ ትስስራቸውን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር እንደሚሰሩ አስታወቁ።
የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) በቻይና መንግስት ምክር ቤት የልማት ምርምር ማዕከል ፕሬዝዳንት ሉ ሃኦ ከተመራ ልዑክ ጋር ዛሬ ተወያይተዋል።
ሚኒስትሩ ከልዑኩ ጋር በኢትዮጵያና ቻይና የንግድ ግንኙነት ዙሪያ ሰፊ ውይይት ማድረጋቸውን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል።
በውይይቱ ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን ጠንካራ የንግድ ግንኙነት ወደ ላቀ ትብብር ማሸጋገር የሚያስችሉ መስኮች መለየታቸውን አመልክተዋል።
በተለይም ኢትዮጵያ ወደ ቻይና የምትልካቸውን ምርቶች ማሳደግና የሁለቱን ሀገራት ኢኮኖሚ ተጠቃሚ የሚያደርጉ ተጨማሪ መስኮችን የዳሰሰ ውጤታማ ውይይት መደረጉን ጠቁመዋል።
ልዑኩ የጥራት መንደርን መጎበኘቱንና ኢትዮጵያ ለጥራት ያላትን ቁርጠኝነት ማሳየት እንደተቻለም ነው ሚኒስትሩ የገለጹት።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025