የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት መስጫ ማዕከል ግንባታ 98 ከመቶ ደርሷል- ግብርና ኮርፖሬሽን</p>

Jan 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 12/207(ኢዜአ)፦ በቦንጋ ከተማ ግንባታ እየተከናወነ የሚገኘው የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት መስጫ ማዕከል ግንባታ 98 ከመቶ መድረሱ የኢትዮጵያ ግብርና ኮርፖሬሽን ገለፀ።

የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ አማካሪ አቶ ካሳሁን ከበደ መንግስት ግብርናን ለማዘመን ከሚያደርጋቸው ጥረቶች መካከል የግብርና ግብዓቶችን በተደራጀ እና በተቀናጀ መልኩ ለአምራቾች ተደራሽ የማድረግ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህም በደቡብ ምዕራብ ቀጠና ተደራሽነቱን በማስፋት በ2012 ዓ.ም ጀምሮ የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት መስጫ ማዕከልግንባታ እየተከናወነ መሆኑን ጠቁመዋል።

በ742 ሚሊየን ብር ወጪ ግንባታ ላይ የሚገኘው ማዕከሉ 98 ከመቶ መድረሱን ገልጸው፤ ግንባታው ሲጠናቀቅ ለአምራቾች የተሟላ የግብርና ግብዓትና የእርሻ ቴክኖሎጂ መሳሪያ ለማቅረብ ትልቅ ሚና ይኖረዋል ብለዋል።

የግብርና ምርትና ምርታማነትን በመጨመር የምግብ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ መንግሥት ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት በቦንጋ ማዕከል በቀጠናው የጥራት ደረጃው የተሻሻሉ ምርጥ ዘር በማምራት ለማቅረብ ትኩረት አድርጎ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

የማዕከሉ ግንባታ በሁለት ሎት ተከፍሎ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው፤ ግንባታው በውስጥ የተለያየ መጠን ያላቸው የእህል ማከማቻ መጋዘኖች፣ ማበጠሪያ ማሽን ክፍሎችና የተለያዩ የኬሚካል ማከማቻ፣ የአስተዳደር ሠራተኛ ቢሮ እንዲሁም የእርሻ ማሽነሪዎች ማከማቻና መስጫ ሼዶች በውስጡ ያካተተ መሆኑን ተናግረዋል።

በኮርፖሬሽኑ የምርጥ ዘርና የደን ውጤቶች ስራ አስፈፃሚ አቶ ዘነበ ወልደሰንበት በበኩላቸው ማዕከሉ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ቴክኖሎጂ በቀጠናው ተደራሽ በማድረግ የግብርና ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ የጎላ ፋይዳ እንዳለው መናገራቸውን ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ኮሙኒኬሸን ቢሮ ያገነኘው መረጃ ያመለክታል።

ኮርፖሬሽኑ የሰብል ዘርን በተለያዩ መንገድ በመሰብሰብ በማዘጋጀትና ደረጃ በማውጣት ለእርሶና ከፍል አርሶ አደሮች እንደሚያቀርብ የገለጹት ስራ አስፈጻሚው እንደሀገር በ2016/17 ምርት ዘመን 465 ሺህ ኩንታል የሚጠጋ የተለያዩ የሰብል ዘር በማባዛት ለአምራቾች ለማቅረብ በ25 ቅርንጫፎቹ በልዩ ትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው &quot;ቡኖ - ማላ&quot; ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026