የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>ኢትዮጵያ ከጂቡቲ ጋር ያላት የጸና ትብብር ለጋራ ዕድገት ምቹ መደላድል የሚፈጥር ነው-ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር)</p>

Jan 21, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ጥር13/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ከጂቡቲ ጋር ያላት የጸና ትብብርና የመሠረተ ልማት ትስስር ለጋራ ዕድገትና ለአዳዲስ ዕድሎች ምቹ መደላድል የሚፈጥር ነው ሲሉ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለፁ፡፡


ሚኒስትሩ፥ ዛሬ በኢትዮ-ሎጅስቲክስ የዘርፍ ማኅበራት በተዘጋጀው የቢዝነስ ማጎልበቻ ኮንፈረንስ ላይ ተገኝተዋል።


በዚህም ከጂቡቲ ጋር ያለውን የንግድ እና ኢንቨስትመንት ግንኙነት አስፈላጊነት እና የኢትዮጵያ መንግስት በቀጣናው የንግድ እድሎችን ለማሳደግ ያለውን ቁርጠኝነት አረጋግጠናል ብለዋል።


ከጂቡቲ ጋር ያለን የጸና ትብብርና የመሠረተ ልማት ትስስር ለጋራ ዕድገትና ለአዳዲስ ዕድሎች ምቹ መደላድል የሚፈጥር መሆኑን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ጠቁመዋል።


የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የንግድ ተግዳሮቶችን በማስወገድ ከአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ስምምነት ጋር የሚስማማና አስተማማኝ የትብብር ማዕቀፍን እውን ለማድረግ በትጋት እየሰራ ነው መሆኑንም ተናግረዋል።


በኢትዮጵያ የማኑፋክቸሪንግና ግብርናን መሰረት ያደረገና ብዝሃነት ያለውን የውጭ ንግድ ለማስፋት ለሚሰራው ስራ ጂቡቲ ስትራቴጂክ አጋር መሆኗን ነው የገለጹት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026