
አዲስ አበባ፤ጥር13/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ከጂቡቲ ጋር ያላት የጸና ትብብርና የመሠረተ ልማት ትስስር ለጋራ ዕድገትና ለአዳዲስ ዕድሎች ምቹ መደላድል የሚፈጥር ነው ሲሉ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለፁ፡፡
ሚኒስትሩ፥ ዛሬ በኢትዮ-ሎጅስቲክስ የዘርፍ ማኅበራት በተዘጋጀው የቢዝነስ ማጎልበቻ ኮንፈረንስ ላይ ተገኝተዋል።
በዚህም ከጂቡቲ ጋር ያለውን የንግድ እና ኢንቨስትመንት ግንኙነት አስፈላጊነት እና የኢትዮጵያ መንግስት በቀጣናው የንግድ እድሎችን ለማሳደግ ያለውን ቁርጠኝነት አረጋግጠናል ብለዋል።
ከጂቡቲ ጋር ያለን የጸና ትብብርና የመሠረተ ልማት ትስስር ለጋራ ዕድገትና ለአዳዲስ ዕድሎች ምቹ መደላድል የሚፈጥር መሆኑን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ጠቁመዋል።
የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የንግድ ተግዳሮቶችን በማስወገድ ከአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ስምምነት ጋር የሚስማማና አስተማማኝ የትብብር ማዕቀፍን እውን ለማድረግ በትጋት እየሰራ ነው መሆኑንም ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ የማኑፋክቸሪንግና ግብርናን መሰረት ያደረገና ብዝሃነት ያለውን የውጭ ንግድ ለማስፋት ለሚሰራው ስራ ጂቡቲ ስትራቴጂክ አጋር መሆኗን ነው የገለጹት።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026