መቀሌ፤ ጥር 13/2017(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የመቀሌ ዲስትሪክት 70 በመቶ ደንበኞቹ ገንዘብ በዲጂታል ቴክኖሎጂ እያንቀሳቀሱ መሆኑን አስታውቋል።
የዲስትሪክቱ ዳይሬክተር አቶ ኤልያስ ልሳነወርቅ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ባንኩ የሞባይል ባንኪንግን ጨምሮ ሌሎች የቴክኖሎጂ አማራጮችን ዘርግቶ በማስተዋወቁ በርካታ ደንበኞቹን የአገልግሎቶቹ ተጠቃሚ ማድረግ ችሏል።
በዲስትሪክቱ በሚገኙ 58 ቅርንጫፎች ስር 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ደንበኞች መኖራቸውን የጠቀሱት አቶ ኤልያስ፤ ከእነዚህ መካከልም 70 በመቶ ያህሉ የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ገንዘባቸውን እያንቀሳቀሱ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በዚህም ገንዘብን ደህንነቱ በተጠቀ ሁኔታ እንዲንቀሳቀስ ዕድል መፍጠሩንም ተናግረዋል።
እንዲሁም ፈጣን የግብይት አገልግሎትን በመፍጠር ጊዜን በአግባቡ ለመጠቀም ያስቻለ መሆኑን ዳይሬክተሩ አስረድተዋል።
በተጨማሪም ደንበኞች ባሉበት ሆነው ሌሎች ስራዎቻቸውን እያከናወኑ ገንዘብ ለማስተላለፍም ሆነ የተለያዩ ክፍያዎችን ለመፈፀም ቴክኖሎጂው እየረዳቸው መሆኑን አቶ ኤልያስ አመልክተዋል።
በቀጣዮቹ ወራትም የዲጂታል አገልግሎት ተጠቃሚ ያልሆኑ ደንበኞቹን ስለ አገልግሎቱ ያላቸውን ግንዛቤ ለማዳበር የተለያዩ የውይይት መድረኮችን ለማካሄድ እቅድ መያዙንም አስታውቀዋል።
የባንኩ የረጅም ጊዜ ደንበኛ መሆናቸውን የሚናገሩት አቶ መሀሪ ፍስሀ፣ ባንኩ የጀመረው የዲጂታል አገልግሎት የገንዘብ ዝውውር ጤናማነትን ስለሚያረጋግጥ መልካም መሆኑን ገልጸዋል።
አገልግሎቱ ፈጣንና አስተማማኝ በመሆኑም ስራቸውን እንዳቀለለላቸው የተናገሩት ደግሞ ሌላው የባንኩ ደንበኛ አቶ አሰፋ ገብረ ስላሴ ናቸው።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025