
መቀሌ፤ ጥር 13/2017(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የመቀሌ ዲስትሪክት 70 በመቶ ደንበኞቹ ገንዘብ በዲጂታል ቴክኖሎጂ እያንቀሳቀሱ መሆኑን አስታውቋል።
የዲስትሪክቱ ዳይሬክተር አቶ ኤልያስ ልሳነወርቅ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ባንኩ የሞባይል ባንኪንግን ጨምሮ ሌሎች የቴክኖሎጂ አማራጮችን ዘርግቶ በማስተዋወቁ በርካታ ደንበኞቹን የአገልግሎቶቹ ተጠቃሚ ማድረግ ችሏል።
በዲስትሪክቱ በሚገኙ 58 ቅርንጫፎች ስር 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ደንበኞች መኖራቸውን የጠቀሱት አቶ ኤልያስ፤ ከእነዚህ መካከልም 70 በመቶ ያህሉ የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ገንዘባቸውን እያንቀሳቀሱ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በዚህም ገንዘብን ደህንነቱ በተጠቀ ሁኔታ እንዲንቀሳቀስ ዕድል መፍጠሩንም ተናግረዋል።
እንዲሁም ፈጣን የግብይት አገልግሎትን በመፍጠር ጊዜን በአግባቡ ለመጠቀም ያስቻለ መሆኑን ዳይሬክተሩ አስረድተዋል።
በተጨማሪም ደንበኞች ባሉበት ሆነው ሌሎች ስራዎቻቸውን እያከናወኑ ገንዘብ ለማስተላለፍም ሆነ የተለያዩ ክፍያዎችን ለመፈፀም ቴክኖሎጂው እየረዳቸው መሆኑን አቶ ኤልያስ አመልክተዋል።
በቀጣዮቹ ወራትም የዲጂታል አገልግሎት ተጠቃሚ ያልሆኑ ደንበኞቹን ስለ አገልግሎቱ ያላቸውን ግንዛቤ ለማዳበር የተለያዩ የውይይት መድረኮችን ለማካሄድ እቅድ መያዙንም አስታውቀዋል።
የባንኩ የረጅም ጊዜ ደንበኛ መሆናቸውን የሚናገሩት አቶ መሀሪ ፍስሀ፣ ባንኩ የጀመረው የዲጂታል አገልግሎት የገንዘብ ዝውውር ጤናማነትን ስለሚያረጋግጥ መልካም መሆኑን ገልጸዋል።
አገልግሎቱ ፈጣንና አስተማማኝ በመሆኑም ስራቸውን እንዳቀለለላቸው የተናገሩት ደግሞ ሌላው የባንኩ ደንበኛ አቶ አሰፋ ገብረ ስላሴ ናቸው።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026