
አዲስ አበባ፤ ጥር 13/2017 (ኢዜአ):- የአልጄሪያ ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ያለውን ምቹ የኢንቨስትመንት እና የንግድ ዕድሎች ተጠቅመው መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ በአልጄሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሙክታር ሙሃመድ ጠየቁ።
አራተኛው ዓለም አቀፍ የግንባታ፣ ኮንስትራክሽን እና የከተማ ልማት ኤግዚቢሽን በአልጄሪያ ምስራቃዊ ክፍል በምትገኘው የአነባ ግዛት ዋና መቀመጫ አነባ ከተማ ተካሄዷል።
በአልጄሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሙክታር ሙሃመድ በኤግዚቢሽኑ ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያና አልጀሪያ በዲፕሎማሲ ረገድ ጠንካራ ግንኙነት ያላቸው አገራት መሆናቸውን አውስተዋል።
የአልጄሪያ ባለሀብቶች በአዲስ አበባ በቀጣይ በሚካሄደው የሁለቱን አገራት የጋራ ኮሚሽን ስብሰባ ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ ጋብዘዋል።
ጉብኝቱ ለድርጅቶቹና ለባለሀብቶቹ በኢትዮጵያ የንግድና ኢንቨስትመንት ዕድሎች ለማየት ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥርላቸው አመልክተዋል።
አምባሳደር ሙክታር ከኤግዚቢሽኑ ጎን ለጎን በተለያዩ በኮንስትራክሽን ግብዓቶች እና ቁሳቁሶች ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ከተሰማሩ የአልጄሪያ ድርጅቶች እና ባለሀብቶች ጋር ተወያይተዋል።
አምባሳደሩ በውይይቱ ስለ ኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት እድሎች ገለጻ ያደረጉ ሲሆን ሚሲዮኑ ለባለሀብቶቹ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።
በኤግዚቢሽኑ ላይ በርካታ ኩባንያዎች ከመደበኛ እስከ ስማርት መኖሪያ ቤቶች እና ሪል ስቴቶች ግብዓት የሚሆኑ ምርቶች እና ግብዓቶች ለእይታ ማቅረባቸውን በአልጀርስ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026