የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>የአልጄሪያ ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ንግድና ኢንቨስትመንት መስኮች እንደሰማሩ ጥሪ ቀረበ</p>

Jan 22, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 13/2017 (ኢዜአ):- የአልጄሪያ ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ያለውን ምቹ የኢንቨስትመንት እና የንግድ ዕድሎች ተጠቅመው መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ በአልጄሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሙክታር ሙሃመድ ጠየቁ።

አራተኛው ዓለም አቀፍ የግንባታ፣ ኮንስትራክሽን እና የከተማ ልማት ኤግዚቢሽን በአልጄሪያ ምስራቃዊ ክፍል በምትገኘው የአነባ ግዛት ዋና መቀመጫ አነባ ከተማ ተካሄዷል።

በአልጄሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሙክታር ሙሃመድ በኤግዚቢሽኑ ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያና አልጀሪያ በዲፕሎማሲ ረገድ ጠንካራ ግንኙነት ያላቸው አገራት መሆናቸውን አውስተዋል።

የአልጄሪያ ባለሀብቶች በአዲስ አበባ በቀጣይ በሚካሄደው የሁለቱን አገራት የጋራ ኮሚሽን ስብሰባ ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ ጋብዘዋል።

ጉብኝቱ ለድርጅቶቹና ለባለሀብቶቹ በኢትዮጵያ የንግድና ኢንቨስትመንት ዕድሎች ለማየት ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥርላቸው አመልክተዋል።

አምባሳደር ሙክታር ከኤግዚቢሽኑ ጎን ለጎን በተለያዩ በኮንስትራክሽን ግብዓቶች እና ቁሳቁሶች ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ከተሰማሩ የአልጄሪያ ድርጅቶች እና ባለሀብቶች ጋር ተወያይተዋል።

አምባሳደሩ በውይይቱ ስለ ኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት እድሎች ገለጻ ያደረጉ ሲሆን ሚሲዮኑ ለባለሀብቶቹ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

በኤግዚቢሽኑ ላይ በርካታ ኩባንያዎች ከመደበኛ እስከ ስማርት መኖሪያ ቤቶች እና ሪል ስቴቶች ግብዓት የሚሆኑ ምርቶች እና ግብዓቶች ለእይታ ማቅረባቸውን በአልጀርስ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026