የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

<p>አየር ኃይል አሁን ለገነባው ከፍተኛ ወታደራዊ የዝግጁነት አቅም የሙያተኛው ድርሻ የጎላ ነው - ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ</p>

Feb 6, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2017(ኢዜአ)፦አየር ኃይል አሁን ለገነባው ከፍተኛ ወታደራዊ የዝግጁነት አቅም የሙያተኛው ድርሻ የጎላ መሆኑን የአየር ሃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ ገለጹ።

የኢፌዴሪ አየር ኃይል ሎጀስቲክስ የእውቅና እና የምስጋና መርሃ-ግብር በአየር ኃይል መኮንኖች ክበብ አካሂዷል።

ዋና አዛዡ በመርሃ-ግብሩ በመገኘት ለተቋሙ የግዳጅ አፈፃፀም ስኬት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ለነበራቸው ክፍሎች የእውቅና እና የምስጋና ሰርተፍኬት ሰጥተዋል።

ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ የአየር ኃይል ሎጀስቲክስ የተቋሙን የማድረግ አቅም ወደ ላቀ ከፍታ ያሸጋገሩ በርካታ ተግባራት ማከናወኑን ጠቅሰው አየር ኃይሉ ለገነባው አሁናዊ ከፍተኛ የዝግጁነት አቅም የክፍሉ ሙያተኞች ድርሻ ከፍተኛ እንደነበረ ተናግረዋል ።

የአየር ኃይል ምክትል አዛዥ ለአየር ሎጀስቲክስ ብርጋዲየር ጄኔራል ነገራ ሌሊሳ በበኩላቸው ተቋሙ አዳዲስ የአቪዬሽን ትጥቆችን ከመታጠቅ ባለፈ ያሉትን ጠግኖ ወደ ግዳጅ በማሰማራት ረገድ ክፍሉ ያከናወነው ተግባር የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል።

በቀጣይነትም በሁሉም መስክ የጀመርናቸውን ስራዎች በላቀ የስራ ተነሳሽነት አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የተሰጣቸውን ግዳጅ እና ተልዕኮ በብቃት ከመፈፀም ባለፈ ችግር ፈቺ የፈጠራ ስራዎችን ለሰሩ ክፍሎች የእውቅና እና የምስጋና ሰርተፊኬት እንደተሰጣቸው ከመከላከያ ሰራዊት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025