የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

<p>ኔዘርላንድስ ኢትዮጵያ ከስደትና ስደት ተመላሾች ጋር በተያያዘ እያከናወነች ያለችውን ጥረት ትደግፋለች</p>

Feb 6, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 28/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ከስደትና ስደት ተመላሾች ጋር በተያያዘ እያከናወነች ያለችውን ጥረት ኔዘርላንድስ እንደምትደግፍ የሀገሪቱ የፍትህና ደህንነት ሚኒስቴር የአለም አቀፍ ጉዳዮች ዳይሬክተር ሮብ ቫን ባህሆቨን ገልፀዋል።

የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት በዋና ዳይሬክተሩ የተመራ ልዑክን ተቀብለው አነጋግረዋል።

በውይይታቸውም ኢትዮጵያ ከስደትና ስደት ተመላሾች ጋር በተያያዘ እያከናወነች ያለችውን ተግባር በሚመለከትና በቀጣይ ከኔዘርላንድስ ጋር በዘርፉ ያሉ ትብብር ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ገለፃ አድርገዋል።


በተጨማሪም ተቋሙ በሪፎርም ሂደት ላይ መሆኑንና የሚሰጡ አገልግሎቶችን በቴክኖሎጂ ለማደራጀት በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ማስረዳታቸውን ከአገልግሎቱ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡

የኔዘርላንድስ የፍትህና ደህነነት ሚኒስቴር የአለም አቀፍ ጉዳዮች ዳይሬክተር ሮብ ቫን ባህሆቨን ኢትዮጵያ ከስደትና ስደት ተመላሾችን በሚመለከት እያከናወነች ያለችው ስራ የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል።

ሀገራቸው በዚህ ረገድ ኢትዮጵያን ለመደገፍ ዝግጁ መሆኗን ማረጋገጣቸውም ተጠቅሷል።

ሁለቱ አካላት በተለይም በአቅም ግንባታ ዘርፍ እና ተቋሙ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ይበልጥ ቀልጣፋ ከማድረግ አኳያ በጋራ ሊሰሩ በሚገቡ ጉዳዮች ላይ መወያየታቸውም ተመላክቷል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025