
አዲስ አበባ፤ ጥር 28/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ከስደትና ስደት ተመላሾች ጋር በተያያዘ እያከናወነች ያለችውን ጥረት ኔዘርላንድስ እንደምትደግፍ የሀገሪቱ የፍትህና ደህንነት ሚኒስቴር የአለም አቀፍ ጉዳዮች ዳይሬክተር ሮብ ቫን ባህሆቨን ገልፀዋል።
የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት በዋና ዳይሬክተሩ የተመራ ልዑክን ተቀብለው አነጋግረዋል።
በውይይታቸውም ኢትዮጵያ ከስደትና ስደት ተመላሾች ጋር በተያያዘ እያከናወነች ያለችውን ተግባር በሚመለከትና በቀጣይ ከኔዘርላንድስ ጋር በዘርፉ ያሉ ትብብር ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ገለፃ አድርገዋል።

በተጨማሪም ተቋሙ በሪፎርም ሂደት ላይ መሆኑንና የሚሰጡ አገልግሎቶችን በቴክኖሎጂ ለማደራጀት በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ማስረዳታቸውን ከአገልግሎቱ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
የኔዘርላንድስ የፍትህና ደህነነት ሚኒስቴር የአለም አቀፍ ጉዳዮች ዳይሬክተር ሮብ ቫን ባህሆቨን ኢትዮጵያ ከስደትና ስደት ተመላሾችን በሚመለከት እያከናወነች ያለችው ስራ የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል።
ሀገራቸው በዚህ ረገድ ኢትዮጵያን ለመደገፍ ዝግጁ መሆኗን ማረጋገጣቸውም ተጠቅሷል።
ሁለቱ አካላት በተለይም በአቅም ግንባታ ዘርፍ እና ተቋሙ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ይበልጥ ቀልጣፋ ከማድረግ አኳያ በጋራ ሊሰሩ በሚገቡ ጉዳዮች ላይ መወያየታቸውም ተመላክቷል፡፡
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026