
አዲስ አበባ፤ ጥር 28/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ከስደትና ስደት ተመላሾች ጋር በተያያዘ እያከናወነች ያለችውን ጥረት ኔዘርላንድስ እንደምትደግፍ የሀገሪቱ የፍትህና ደህንነት ሚኒስቴር የአለም አቀፍ ጉዳዮች ዳይሬክተር ሮብ ቫን ባህሆቨን ገልፀዋል።
የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት በዋና ዳይሬክተሩ የተመራ ልዑክን ተቀብለው አነጋግረዋል።
በውይይታቸውም ኢትዮጵያ ከስደትና ስደት ተመላሾች ጋር በተያያዘ እያከናወነች ያለችውን ተግባር በሚመለከትና በቀጣይ ከኔዘርላንድስ ጋር በዘርፉ ያሉ ትብብር ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ገለፃ አድርገዋል።

በተጨማሪም ተቋሙ በሪፎርም ሂደት ላይ መሆኑንና የሚሰጡ አገልግሎቶችን በቴክኖሎጂ ለማደራጀት በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ማስረዳታቸውን ከአገልግሎቱ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
የኔዘርላንድስ የፍትህና ደህነነት ሚኒስቴር የአለም አቀፍ ጉዳዮች ዳይሬክተር ሮብ ቫን ባህሆቨን ኢትዮጵያ ከስደትና ስደት ተመላሾችን በሚመለከት እያከናወነች ያለችው ስራ የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል።
ሀገራቸው በዚህ ረገድ ኢትዮጵያን ለመደገፍ ዝግጁ መሆኗን ማረጋገጣቸውም ተጠቅሷል።
ሁለቱ አካላት በተለይም በአቅም ግንባታ ዘርፍ እና ተቋሙ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ይበልጥ ቀልጣፋ ከማድረግ አኳያ በጋራ ሊሰሩ በሚገቡ ጉዳዮች ላይ መወያየታቸውም ተመላክቷል፡፡
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026