
አዲስ አበባ፤ ጥር 28/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ከስደትና ስደት ተመላሾች ጋር በተያያዘ እያከናወነች ያለችውን ጥረት ኔዘርላንድስ እንደምትደግፍ የሀገሪቱ የፍትህና ደህንነት ሚኒስቴር የአለም አቀፍ ጉዳዮች ዳይሬክተር ሮብ ቫን ባህሆቨን ገልፀዋል።
የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት በዋና ዳይሬክተሩ የተመራ ልዑክን ተቀብለው አነጋግረዋል።
በውይይታቸውም ኢትዮጵያ ከስደትና ስደት ተመላሾች ጋር በተያያዘ እያከናወነች ያለችውን ተግባር በሚመለከትና በቀጣይ ከኔዘርላንድስ ጋር በዘርፉ ያሉ ትብብር ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ገለፃ አድርገዋል።

በተጨማሪም ተቋሙ በሪፎርም ሂደት ላይ መሆኑንና የሚሰጡ አገልግሎቶችን በቴክኖሎጂ ለማደራጀት በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ማስረዳታቸውን ከአገልግሎቱ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
የኔዘርላንድስ የፍትህና ደህነነት ሚኒስቴር የአለም አቀፍ ጉዳዮች ዳይሬክተር ሮብ ቫን ባህሆቨን ኢትዮጵያ ከስደትና ስደት ተመላሾችን በሚመለከት እያከናወነች ያለችው ስራ የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል።
ሀገራቸው በዚህ ረገድ ኢትዮጵያን ለመደገፍ ዝግጁ መሆኗን ማረጋገጣቸውም ተጠቅሷል።
ሁለቱ አካላት በተለይም በአቅም ግንባታ ዘርፍ እና ተቋሙ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ይበልጥ ቀልጣፋ ከማድረግ አኳያ በጋራ ሊሰሩ በሚገቡ ጉዳዮች ላይ መወያየታቸውም ተመላክቷል፡፡
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026