የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

<p>በባህርዳር ከተማ የኢንተርፕራይዞች ኤግዚቢሽንና ባዛር ተከፈተ</p>

Feb 6, 2025

IDOPRESS

ባህር ዳር ፤ጥር 28/2017 (ኢዜአ)፡- በባህር ዳር ከተማ የኢንተርፕራይዞችን ምርት ለተጠቃሚው ማህበረሰብ በስፋት ለማድረስና የገበያ ትስሰር መፍጠርን ዓላማ ያደረገ ኤግዚቢሽንና ባዛር ተከፈተ።

ጥርን በባህር ዳር አካል የሆነው የማጠቃለያ የኢንተርፕራይዞች ኤግዚቢሽንና ባዛር ዛሬ ተከፍቷል።

የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ አስሜ ብርሌ እንደገለጹት፤ መንግስት የኢንተርፕራይዞችን የገበያ ችግር ለመፍታት ከሰጣቸው ትኩረቶች አንዱ የገበያ ትስስር መፍጠር ነው።


ለዚህም ኤግዚቢሽኖችና ባዛሮችን በማዘጋጀት ኢንተርፕራይዞች ምርትና አገልግሎታቸውን ለተጠቃሚው ህብረተሰብ እንዲያቀርቡ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

የከተማው ህብረተሰብም በተለያዩ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች የሚያመርቷቸውን ምርቶች በመግዛት ሊያበረታታ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የከተማ አስተዳደሩ ስራና ስልጠና መምሪያ ኃላፊ አቶ ዘመነ አሰፋ በበኩላቸው "ለኢንተርፕራይዞች በዓመት እስከ ሦስት ጊዜ ኤግዚቢሽንና ባዛር በማዘጋጀት ሸማችና ሻጩን በአንድ መድረክ በማገናኘት የገበያ ትስስር ለመፍጠር እየተሰራ ይገኛል " ብለዋል።


ኤግዚቢሽንና ባዛሩ ከዛሬ ጀምሮ እስከ የካቲት 2 ቀን 2017 ዓም እንደሚቆይ ጠቁመው 47 ኢንተርፕራይዞች ምርቶቻቸውን ይዘው መቅረባቸውን ተናግረዋል።

በኤግዚቢሽንና ባዛሩ ያመረቷቸውን ባህላዊ አልባሳት ይዘው መቅረባቸውን የገለፁት ደግሞ ወይዘሪት ነፃነት አጠቃ ናቸው።


በሦስት ሺህ ብር መነሻ ካፒታል ከሦስት ዓመት በፊት የጀመሩት ስራ አሁን ላይ ካፒታላቸውን ወደ አንድ ሚሊዮን ብር ማሳደጋቸውን ተናግረዋል።

ወጣት ይበልጣል በላይነህ በበኩሉ የሚዘጋጁ ኤግዚቢሽንና ባዛሮች የገበያ ችግሮቻቸውን በትስስር ለመፍታት ምቹ ሁኔታ መፍጠራቸውን ገልጿል።

በ2014 ዓ.ም በግማሽ ሚሊዮን ብር መነሻ ካፒታል የጀመረው የጫማ ስራ አሁን ላይ ካፒታሉን 7 ሚሊዮን ብር ማድረሱን አስታውቋል።

የጥርን በባህር ዳር ማጠቃለያ በሆነው ኤግዚቢሽንና ባዛር በጨርቃጨርቅና አልባሳት፣ በቆዳና ቆዳ ውጤቶች፣ በግብርና፣ በኢንዱስትሪና ሌሎች ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025