አዲስ አበባ፤ ጥር 29/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት በተመራማሪዎቹ ያሰራቸውን የእንጨትና የብረት ቅርጽ ማውጫ ማሽኖች ለአምስት ክልሎች አስረከበ።
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አብዲሳ ይልማ በርክክቡ ወቅት እንደገለጹት፤ ማሽኖቹ በተቋሙ ባለሙያዎች የለሙና በራስ አቅም የተሰሩ ናቸው።
በኢንስቲትዩቱ የተሰሩ አምስት የፕላዝማ እና ራውተር ሲ. ኤን. ሲ ማሽኖችን ለአማራ፣ ትግራይ፣ ሲዳማ፣ አፋር እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ነው ያስረከበው።
ማሽኖቹ በብረትና እንጨት ላይ ቅርጾችን ለማውጣት የሚያገለግሉ መሆናቸውን ገልጸው፤ በክልሎች ለወጣቶች የስራ እድል ፈጠራ የሚውሉ መሆኑንም ተናግረዋል።
በማሽኖቹ የሚጠቀሙት ዜጎች ቴክኖሎጂውን በማልማትና በማባዛት በሺዎች የሚቆጠሩ የስራ እድሎችን መፍጠር እንዳለባቸው ነው ያሳሰቡት።
ኢንስቲትዩቱ በአሁኑ ወቅት በሰው ሃይል፣ በአደረጃጀት እና በቴክኖሎጂ የውስጥ አቅሙን በማሳደግ ለአገልግሎት ፈላጊዎች ተደራሽ ለመሆን እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
በተያዘው አመት የስፔስና የጂኦስፓሻል መረጃዎችን ጥቅም ላይ ከማዋል አኳያም በርካታ ሴክተሮችን መመስረቱን አንሰተዋል።
የክልሎቹ ተወካዮች በበኩላቸው ኢንስቲትዩቱ ማሽኖቹን ከማስረከብ ባለፈ በአጠቃቀሙ ላይ ስልጠና እንዲወስዱ ማድረጉን ተናግረዋል።
ኢንስቲትዩቱ ቴክኖሎጂውን ጥቅም ላይ ከማዋል ባለፈም ቀጣይነት ያለው ክትትልና ድጋፍ እንዲያደርግላቸውም ነው የጠቆሙ።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025