
አዲስ አበባ፤ ጥር 29/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት በተመራማሪዎቹ ያሰራቸውን የእንጨትና የብረት ቅርጽ ማውጫ ማሽኖች ለአምስት ክልሎች አስረከበ።

የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አብዲሳ ይልማ በርክክቡ ወቅት እንደገለጹት፤ ማሽኖቹ በተቋሙ ባለሙያዎች የለሙና በራስ አቅም የተሰሩ ናቸው።
በኢንስቲትዩቱ የተሰሩ አምስት የፕላዝማ እና ራውተር ሲ. ኤን. ሲ ማሽኖችን ለአማራ፣ ትግራይ፣ ሲዳማ፣ አፋር እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ነው ያስረከበው።
ማሽኖቹ በብረትና እንጨት ላይ ቅርጾችን ለማውጣት የሚያገለግሉ መሆናቸውን ገልጸው፤ በክልሎች ለወጣቶች የስራ እድል ፈጠራ የሚውሉ መሆኑንም ተናግረዋል።
በማሽኖቹ የሚጠቀሙት ዜጎች ቴክኖሎጂውን በማልማትና በማባዛት በሺዎች የሚቆጠሩ የስራ እድሎችን መፍጠር እንዳለባቸው ነው ያሳሰቡት።
ኢንስቲትዩቱ በአሁኑ ወቅት በሰው ሃይል፣ በአደረጃጀት እና በቴክኖሎጂ የውስጥ አቅሙን በማሳደግ ለአገልግሎት ፈላጊዎች ተደራሽ ለመሆን እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
በተያዘው አመት የስፔስና የጂኦስፓሻል መረጃዎችን ጥቅም ላይ ከማዋል አኳያም በርካታ ሴክተሮችን መመስረቱን አንሰተዋል።
የክልሎቹ ተወካዮች በበኩላቸው ኢንስቲትዩቱ ማሽኖቹን ከማስረከብ ባለፈ በአጠቃቀሙ ላይ ስልጠና እንዲወስዱ ማድረጉን ተናግረዋል።
ኢንስቲትዩቱ ቴክኖሎጂውን ጥቅም ላይ ከማዋል ባለፈም ቀጣይነት ያለው ክትትልና ድጋፍ እንዲያደርግላቸውም ነው የጠቆሙ።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026