
አዲስ አበባ፤ ጥር 29/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት በተመራማሪዎቹ ያሰራቸውን የእንጨትና የብረት ቅርጽ ማውጫ ማሽኖች ለአምስት ክልሎች አስረከበ።

የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አብዲሳ ይልማ በርክክቡ ወቅት እንደገለጹት፤ ማሽኖቹ በተቋሙ ባለሙያዎች የለሙና በራስ አቅም የተሰሩ ናቸው።
በኢንስቲትዩቱ የተሰሩ አምስት የፕላዝማ እና ራውተር ሲ. ኤን. ሲ ማሽኖችን ለአማራ፣ ትግራይ፣ ሲዳማ፣ አፋር እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ነው ያስረከበው።
ማሽኖቹ በብረትና እንጨት ላይ ቅርጾችን ለማውጣት የሚያገለግሉ መሆናቸውን ገልጸው፤ በክልሎች ለወጣቶች የስራ እድል ፈጠራ የሚውሉ መሆኑንም ተናግረዋል።
በማሽኖቹ የሚጠቀሙት ዜጎች ቴክኖሎጂውን በማልማትና በማባዛት በሺዎች የሚቆጠሩ የስራ እድሎችን መፍጠር እንዳለባቸው ነው ያሳሰቡት።
ኢንስቲትዩቱ በአሁኑ ወቅት በሰው ሃይል፣ በአደረጃጀት እና በቴክኖሎጂ የውስጥ አቅሙን በማሳደግ ለአገልግሎት ፈላጊዎች ተደራሽ ለመሆን እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
በተያዘው አመት የስፔስና የጂኦስፓሻል መረጃዎችን ጥቅም ላይ ከማዋል አኳያም በርካታ ሴክተሮችን መመስረቱን አንሰተዋል።
የክልሎቹ ተወካዮች በበኩላቸው ኢንስቲትዩቱ ማሽኖቹን ከማስረከብ ባለፈ በአጠቃቀሙ ላይ ስልጠና እንዲወስዱ ማድረጉን ተናግረዋል።
ኢንስቲትዩቱ ቴክኖሎጂውን ጥቅም ላይ ከማዋል ባለፈም ቀጣይነት ያለው ክትትልና ድጋፍ እንዲያደርግላቸውም ነው የጠቆሙ።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026