
አዲስ አበባ፤ ጥር 29/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት በተመራማሪዎቹ ያሰራቸውን የእንጨትና የብረት ቅርጽ ማውጫ ማሽኖች ለአምስት ክልሎች አስረከበ።

የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አብዲሳ ይልማ በርክክቡ ወቅት እንደገለጹት፤ ማሽኖቹ በተቋሙ ባለሙያዎች የለሙና በራስ አቅም የተሰሩ ናቸው።
በኢንስቲትዩቱ የተሰሩ አምስት የፕላዝማ እና ራውተር ሲ. ኤን. ሲ ማሽኖችን ለአማራ፣ ትግራይ፣ ሲዳማ፣ አፋር እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ነው ያስረከበው።
ማሽኖቹ በብረትና እንጨት ላይ ቅርጾችን ለማውጣት የሚያገለግሉ መሆናቸውን ገልጸው፤ በክልሎች ለወጣቶች የስራ እድል ፈጠራ የሚውሉ መሆኑንም ተናግረዋል።
በማሽኖቹ የሚጠቀሙት ዜጎች ቴክኖሎጂውን በማልማትና በማባዛት በሺዎች የሚቆጠሩ የስራ እድሎችን መፍጠር እንዳለባቸው ነው ያሳሰቡት።
ኢንስቲትዩቱ በአሁኑ ወቅት በሰው ሃይል፣ በአደረጃጀት እና በቴክኖሎጂ የውስጥ አቅሙን በማሳደግ ለአገልግሎት ፈላጊዎች ተደራሽ ለመሆን እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
በተያዘው አመት የስፔስና የጂኦስፓሻል መረጃዎችን ጥቅም ላይ ከማዋል አኳያም በርካታ ሴክተሮችን መመስረቱን አንሰተዋል።
የክልሎቹ ተወካዮች በበኩላቸው ኢንስቲትዩቱ ማሽኖቹን ከማስረከብ ባለፈ በአጠቃቀሙ ላይ ስልጠና እንዲወስዱ ማድረጉን ተናግረዋል።
ኢንስቲትዩቱ ቴክኖሎጂውን ጥቅም ላይ ከማዋል ባለፈም ቀጣይነት ያለው ክትትልና ድጋፍ እንዲያደርግላቸውም ነው የጠቆሙ።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026