የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>በክልሉ ያለውን የመልማት አቅም በመለየት ለውጥ ለማምጣት ርብርብ ይደረጋል - ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር)</p>

Feb 7, 2025

IDOPRESS

ቦንጋ፤ ጥር 29/2017(ኢዜአ)፡- በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ያለውን የመልማት አቅም በመለየትና በተደራጀ አግባብ በመምራት ለውጥ ለማምጣት ርብርብ እንደሚደረግ የክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ።

"ከእምቅ አቅም ወደ ሚጨበጥ ሃብት" በሚል መሪ ሀሳብ በክልሉ በቀጣይ ሶስት ዓመታት የሚተገበሩ የልማት አቅጣጫዎች ታሳቢ ተደርጎ በተዘጋጀ የዕቅድ ሰነድ ላይ ውይይት ተካሂዷል።

የውይይት መድረኩን የመሩት ምክትል ርዕሰ መስተዳደሩ፤ ዕቅዱ በክልሉ በሁሉም ዘርፍ ያለውን እምቅ የመልማት አቅም በተደራጀ መልኩ ወደ ሀብትነት መቀየር የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።


ለዚህም ከሀገራዊው በተጨማሪ አዳዲስ ክልላዊ ኢንሼቲቮች መለየታቸውን አንስተው፣ በዚህም ያለንን አቅም በተገቢው ተጠቅመን ተጨባጭ ለውጥ ለማምጣት በልዩ ትኩረት እንሰራለን ብለዋል።

ክልሉ የሚታወቅባቸውንና ለሀገር ኢኮኖሚም ትልቅ ፋይዳ ያላቸው የቡና፣ የሻይ፣ ቅመማቅመም፣ የአትክልትና ፍራፍሬ፣ የእንሰት ልማት ማስፋትና ጥራቱን ማስጠበቅ ላይ በላቀ ቁርጠኝነት ይሰራል ሲሉም ጠቅሰዋል።

የመስኖ ልማትን ማጠናከር፣ የአርሶና አርብቶ አደር ቁጠባን ማዳበር፣ የመሬት አስተዳደርን ማጠናከር፣ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት፣ የማዕድን ሀብቶችን በልዩ ንቅናቄ መምራት ከተያዙ አቅጣጫዎች መካከል እንደሚገኙበት አመላክተዋል።

በሚዘጋጁ ሕዝባዊ የውይይት መድረኮች ጠንካራ ድጋፍና ክትትል በማድረግ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታት ሌላኛው ነው ብለዋል።

በዚህም ለሕዝቡ የገባነውን ቃል ወደ ተግባር በመቀየር ተጠቃሚነቱን ማሳደግ እንደሚገባም ተናግረዋል።


የክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሀላፊ አቶ የሺዋስ አለሙ በበኩላቸው፤ ክልሉ ያለውን ሀብት በተደራጀና አቅምን ባገናዘበ መልኩ ወደ ልማት ባለመገባቱ የተፈለገውን ውጤት ማምጣት አልተቻለም ብለዋል።

ዕቅዱ ከተረጂነት የሚያላቅቅና እራሱን የሚለውጥ ማህበረሰብ የመፍጠር እሳቤ ያለው መሆኑን አመልክተው፤ በዚህም አርሶና አርብቶ አደሩ ሀብቱን ወደ ልማት በመቀየር ተጠቃሚ እንዲሆን የሚያስችል እንደሆነ ተናግረዋል።

ሰነዱ ያለንን ሀብት አውጥቶ ያሳየና ወደ ተሻለ ስራ የሚያስገባ ነው ያሉት ደግሞ የመድረኩ ተሳታፊ በብልፅግና ፖርቲ የካፋ ዞን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ አጥናፉ ሀይሌ ናቸው።

ከዚህ ቀደም በተበታተነ መልኩ ይሰራ የነበረውን በተደራጀ አኳን ለመተግባር ያስችላል ብለዋል።

ከዚህ አንፃርም እንደ አካባቢው ተጨባጭ ሁኔታ በመለየት ውጤታማ በሚያደርግ መልኩ የተቀመጡ ተግባራትን ለመፈፀም ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው &quot;ቡኖ - ማላ&quot; ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026