
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፦የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባ የፕላስቲክ ፎርምወርክ የግንባታ ግብዓት ማምረቻ ፋብሪካን መርቀው ስራ አስጀመሩ።
ፋብሪካው ገቢ ምርትን በመተካት በዓመት ከ15 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሪ የማዳን አቅም እንዳለው ተገልጿል።
የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል በዚሁ ወቅት እንዳሉት ለአምራች ኢንዱስትሪ በልዩ ትኩረት የፖሊሲ እና የህግ ማእቀፎችን በማሻሻል ውጤታማ ስራዎች እየተከናወኑ ነው፡፡
ለዘርፉ ሁሉን አቀፍ ድጋፍ እና ክትትል በማድረግ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የተረጋጋ ኢኮኖሚ ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
ምርትን ለውጭ ገበያ የሚያቀርቡ ጠንካራና ተወዳዳሪ ኢንዱስትሪ መገንባት የሚቻለው ወደ ሀገር የሚገባ ምርትን የሚተኩ ኢንዱስትሪዎችን በመደገፍ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
ዛሬ የተመረቀው ፋብሪካም ተኪ ምርትን በማስፋትና የሀገራዊ ፖሊሲን በማሳካት ረገድ ትልቅ ሚና እንደሚኖረው አንስተዋል።
ፋብሪካው በሀገራችን የእንጨት ፎርምዎርኮችን በፕላስቲክ መተካት መቻሉ ኢትዮጵያ የጀመረችውን የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ከመደገፍ አኳያ ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ጠቁመዋል።
በተለይም የደን ጭፍጨፋን የሚታደግ እና የግንባታ ዘርፉን ተወዳዳሪነት የሚጨምር መሆኑንም አመላክተዋል።
ከውጪ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት የውጪ ምንዛሬን በማዳን፣ ለዜጎች ተጨማሪ የስራ እድል በመፍጠር ለሀገር ኢኮኖሚ እድገት ሚና ላላቸው ፋብሪካዎች ሚኒስቴሩ ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
የኤች ኬ ቢዝነስ ግሩፕ ስራ አስፈጻሚና ባለቤት ካሳነሽ አያሌው በበኩላቸው፥ ፋብሪካው በድጋሚ ጥቅም ላይ የሚውል የግንባታ ፕላስቲክ ፎርምዎርክ አምርቶ ለሀገር ውስጥ እና ለውጭ ገበያ ለማቅረብ መዘጋጀቱን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ በየዓመቱ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞች እየተከለች ቢሆንም በሌላ በኩል ለእንጨት ፎርምዎርክ መስሪያ ዛፎች እንደሚቆረጡ አንስተዋል።
የፕላስቲክ ፎርምዎርኩ ከእንጨት የሚሰራ የግንባታ ግብዓትን በመተካት የደን መጨፍጨፍን ለመቀነስ እንደሚያግዝም ጠቁመዋል።
ምርቶቹ በሀገራችን ውስጥ መመረታቸው ከውጭ የሚገባውን ተመሳሳይ ምርት በመተካት በዓመት ከ15 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሪ ማስቀረት የሚችል መሆኑ ተገልጿል፡፡
ከአዲስ የፕላስቲክ ጥሬ እቃ በተጨማሪ የወዳደቁ የፕላስቲክ ውጤቶችን በግብዓትነት መልሶ ጥቅም ላይ የሚያውል በመሆኑ የአካባቢ ብክለትን ለመቀነስ እንደሚያግዝ ተጠቁሟል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026