
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፦የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባ የፕላስቲክ ፎርምወርክ የግንባታ ግብዓት ማምረቻ ፋብሪካን መርቀው ስራ አስጀመሩ።
ፋብሪካው ገቢ ምርትን በመተካት በዓመት ከ15 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሪ የማዳን አቅም እንዳለው ተገልጿል።
የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል በዚሁ ወቅት እንዳሉት ለአምራች ኢንዱስትሪ በልዩ ትኩረት የፖሊሲ እና የህግ ማእቀፎችን በማሻሻል ውጤታማ ስራዎች እየተከናወኑ ነው፡፡
ለዘርፉ ሁሉን አቀፍ ድጋፍ እና ክትትል በማድረግ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የተረጋጋ ኢኮኖሚ ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
ምርትን ለውጭ ገበያ የሚያቀርቡ ጠንካራና ተወዳዳሪ ኢንዱስትሪ መገንባት የሚቻለው ወደ ሀገር የሚገባ ምርትን የሚተኩ ኢንዱስትሪዎችን በመደገፍ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
ዛሬ የተመረቀው ፋብሪካም ተኪ ምርትን በማስፋትና የሀገራዊ ፖሊሲን በማሳካት ረገድ ትልቅ ሚና እንደሚኖረው አንስተዋል።
ፋብሪካው በሀገራችን የእንጨት ፎርምዎርኮችን በፕላስቲክ መተካት መቻሉ ኢትዮጵያ የጀመረችውን የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ከመደገፍ አኳያ ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ጠቁመዋል።
በተለይም የደን ጭፍጨፋን የሚታደግ እና የግንባታ ዘርፉን ተወዳዳሪነት የሚጨምር መሆኑንም አመላክተዋል።
ከውጪ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት የውጪ ምንዛሬን በማዳን፣ ለዜጎች ተጨማሪ የስራ እድል በመፍጠር ለሀገር ኢኮኖሚ እድገት ሚና ላላቸው ፋብሪካዎች ሚኒስቴሩ ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
የኤች ኬ ቢዝነስ ግሩፕ ስራ አስፈጻሚና ባለቤት ካሳነሽ አያሌው በበኩላቸው፥ ፋብሪካው በድጋሚ ጥቅም ላይ የሚውል የግንባታ ፕላስቲክ ፎርምዎርክ አምርቶ ለሀገር ውስጥ እና ለውጭ ገበያ ለማቅረብ መዘጋጀቱን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ በየዓመቱ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞች እየተከለች ቢሆንም በሌላ በኩል ለእንጨት ፎርምዎርክ መስሪያ ዛፎች እንደሚቆረጡ አንስተዋል።
የፕላስቲክ ፎርምዎርኩ ከእንጨት የሚሰራ የግንባታ ግብዓትን በመተካት የደን መጨፍጨፍን ለመቀነስ እንደሚያግዝም ጠቁመዋል።
ምርቶቹ በሀገራችን ውስጥ መመረታቸው ከውጭ የሚገባውን ተመሳሳይ ምርት በመተካት በዓመት ከ15 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሪ ማስቀረት የሚችል መሆኑ ተገልጿል፡፡
ከአዲስ የፕላስቲክ ጥሬ እቃ በተጨማሪ የወዳደቁ የፕላስቲክ ውጤቶችን በግብዓትነት መልሶ ጥቅም ላይ የሚያውል በመሆኑ የአካባቢ ብክለትን ለመቀነስ እንደሚያግዝ ተጠቁሟል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026