
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን እድገትና ብልጽግና የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥሉ የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ገለጹ።
የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ያዘጋጀው ሀገር አቀፍ የመንገድ ዘርፍ ጉባዔ ዛሬ በጎንደር ከተማ ተካሂዷል።
በጉባዔው ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የከተማ፣ መሠረተ-ልማት እና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት፣ የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን(ዶ/ር)፣ የክልል የዘርፉ አመራሮች እና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ እንዳሉት መንግስት ለከተሞች በሰጠው ልዩ ትኩረት በ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድ የመንገድ ዘርፉን ለማሳደግና የገጠሩን ማህበረሰብ ከከተማ ነዋሪው ጋር ለማስተሳሰር የተለያዩ ተግባራት ተከናውነዋል።
በዚህም የሀገርን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ለማረጋገጥ በተሰራው ስራ አመርቂ ውጤት ተመዝግቧል ብለዋል።
በዚህም የመንገድ ሽፋንን በሀገር አቀፍ ደረጃ ከለውጡ በፊት ከነበረበት 126 ሺህ ኪሎ ሜትር ወደ 171 ሺህ ነጥብ 18 ኪሎ ሜትር ማሳደግ መቻሉን ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያን እድገት እና ልማት የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላሉ ብለዋል ሚኒስትሯ በንግግራቸው።
በመንገድ ዘርፍ የህዝብ ለህዝብ ትስስርን ለማሳደግ እና ለህብረተሰቡ ጥያቄ ፈጣን ምላሽ በመስጠት ዘላቂነትንና ፍትሃዊነትን በየጊዜው በማረጋገጥ በ2030 ኢትዮጵያን የአፍሪካ የብልጽግና ማዕከል ለማድረግ ይሰራል ነው ያሉት።

የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን(ዶ/ር) በበኩላቸው መንግስት ለመንገድ ዘርፍ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው ብለዋል።
በዚህም የክልሉን የመንገድ ሽፋን በማሳደግ እድገትን ለማፈጠን እየተሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል።
በፎረሙ የሀገር እና ክልል አቀፍ የመንገድ እና መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ላይ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
የቅንጅት አሰራርን ለማጠናከር ያለመ የመንገድ ዘርፍ ፎረም መመስረቱንም ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026