አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፦ ስምንተኛው የአፍሪካ ቢዝነስ ፎረም የካቲት 10 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይከናወናል።
ፎረሙ የሚካሄደው “ከእመርታ ወደ ብልጽግና፤ የአፍሪካን ቀጣናዊ የእሴት ሰንሰለቶች አቅም ማጠናከር” በሚል መሪ ሀሳብ ነው።
የቢዝነስ ፎረሙ በአፍሪካ የቁም እንስሳት፣ ግብርና እና ፋርማሲዩቲካል ዘርፎች ቀጣናዊ የእሴት ሰንሰለት እና ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች ልማት ላይ ያተኮረ መሆኑን ኢዜአ ከተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
መንግስታት፣ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች፣ የፋይናንስ ተቋማት እና የግሉ ዘርፍ በአፍሪካ እሴትን በመጨመር፣ በዘላቂ የኢንዱስትሪ ልማት፣ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ አጠቃቀም፣ የስራ እድል ፈጠራ እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እያከናወኑት ያለው ስራ ውይይት ይደረግበታል።
ፎረሙ ለቀጣናዊ እሴት ሰንሰለት እና ልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች ልማት የኢንቨስትመንት ሀብት ማሰባሰብ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይም ይመክራል።
የአፍሪካ የቢዝነስ ፎረም እ.አ.አ ከ2018 አንስቶ በመካሄድ ላይ ይገኛል።
ፎረሙ በመንግስታት፣ ባለሀብቶች፣ ፕሮጀክት አስተባባሪዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት መካከል የዘላቂ ልማት ግቦች እና የአጀንዳ 2063 ውጥኖችን ለማሳካት ያሉ እድሎች፣ ፈተናዎች እና ተግባራዊ ምላሾች ላይ እንዲወያዩ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ኮሚሽኑ ገልጿል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025