የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>ዓመታዊው የአፍሪካ የቢዝነስ ፎረም በአዲስ አበባ ይካሄዳል</p>

Feb 8, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፦ ስምንተኛው የአፍሪካ ቢዝነስ ፎረም የካቲት 10 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይከናወናል።

ፎረሙ የሚካሄደው “ከእመርታ ወደ ብልጽግና፤ የአፍሪካን ቀጣናዊ የእሴት ሰንሰለቶች አቅም ማጠናከር” በሚል መሪ ሀሳብ ነው።

የቢዝነስ ፎረሙ በአፍሪካ የቁም እንስሳት፣ ግብርና እና ፋርማሲዩቲካል ዘርፎች ቀጣናዊ የእሴት ሰንሰለት እና ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች ልማት ላይ ያተኮረ መሆኑን ኢዜአ ከተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

መንግስታት፣ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች፣ የፋይናንስ ተቋማት እና የግሉ ዘርፍ በአፍሪካ እሴትን በመጨመር፣ በዘላቂ የኢንዱስትሪ ልማት፣ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ አጠቃቀም፣ የስራ እድል ፈጠራ እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እያከናወኑት ያለው ስራ ውይይት ይደረግበታል።

ፎረሙ ለቀጣናዊ እሴት ሰንሰለት እና ልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች ልማት የኢንቨስትመንት ሀብት ማሰባሰብ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይም ይመክራል።

የአፍሪካ የቢዝነስ ፎረም እ.አ.አ ከ2018 አንስቶ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

ፎረሙ በመንግስታት፣ ባለሀብቶች፣ ፕሮጀክት አስተባባሪዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት መካከል የዘላቂ ልማት ግቦች እና የአጀንዳ 2063 ውጥኖችን ለማሳካት ያሉ እድሎች፣ ፈተናዎች እና ተግባራዊ ምላሾች ላይ እንዲወያዩ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ኮሚሽኑ ገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው &quot;ቡኖ - ማላ&quot; ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026