የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>ምክር ቤቱ ለፌዴራል ዋና ኦዲተር የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ ይቀጥላል - ምክትል አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ሎሚ በዶ</p>

Feb 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የፌዴራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት የህዝብን ውስን ሀብት በቁጠባና ውጤታማ በሆነ መንገድ ለህዝብ አገልግሎት ተደራሽ መሆኑን የሚያረጋግጥ ተቋም እንዲሆን ምክር ቤቱ ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባዔ ወይዘሮ ሎሚ በዶ ገልፀዋል።

ምክትል አፈ ጉባኤዋ የፌዴራል ዋና ኦዲተር 80ኛ አመት የምስረታ መታሰቢያ በዓልና የሕንጻ እድሳት ምረቃ ፕሮግራም ላይ ተገኝተው መልዕክት አስተላልፈዋል።


በመልዕክታቸውም ለአንድ ሀገር እድገትና ብልጽግና በተለያዩ የስራ ዘርፎች ተሰማርተው ተልዕኳቸውን የሚወጡ የመንግስት ተቋማት የሚያበረክቱት ሁለንተናዊ አስተዋጽኦ መሠረታዊ ጉዳይ ነው ብለዋል።

በተለይም ለህብረተሰቡና ለሀገር የተለያዩ አገልግሎቶችን በማቅረብ የተጣለባቸውን ተግባርና ኃላፊነት የሚወጡ ተቋማት መንግስትና አሠራር በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት እንዲያገኙ በማድረግ ረገድ የሚጫወቱት ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ተቋማት ለህገ ወጥ አሠራር እንዳይጋለጡና በጀትና ሌሎች ግብዓቶች ለብክነት ሳይጋለጡ፤ ህግና አሠራር ተከትለው ለሚፈለገው አላማ እንዲውል እንዲሁም ብልሹ አሠራሮች እንዲታረሙና ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ የተቆጣጣሪ ተቋማትን አቅም መገንባት አስፈላጊ ነው ብለዋል።

ተቋሙ በተሰጡት ስልጣንና ተግባሮች የተቋማትን የበጀትና ንብረት አጠቃቀም እና አያያዝ ህጋዊነት ነጻና ገለልተኛ በሆነ መርህ በማረጋገጥ የተጠያቂነትና የግልጽነት አሠራር እንዲሰፍን በማድረግ የበኩሉን ሚና ሲወጣ ቆይቷል ነው ያሉት፡፡

የተለያዩ ተቋማትን አሠራር በመቆጣጠርና በመመርመር እንዲሁም የታዩ የአሠራር ችግሮችን በተለያዩ ኦዲቶች ነቅሶ በማውጣትና እንዲስተካከሉ በማድረግ የግልጽነትና የተጠያቂነት አሠራርን በማረጋገጥ ውጤታማ ስራ በማከናወን ላይ እንደሚገኝም ተናግረዋል፡፡


የተቋሙ የኦዲት አሠራር ወጥና አለም አቀፍ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ ከፌዴራል ተቋማት አልፎ ሀገራዊ እንዲሆን ለማድረግና፤ ኦዲቱ የተሻለ ደረጃ ላይ ለማድረስ የሚያስችሉትን ቅንጅታዊ አሠራሮችን በመከተል ላይ እንደሚገኝም እንስተዋል።

ምክር ቤቱ ተቋሙ ተልዕኮውን ለማሳካት በሚያደርገው እንቅስቃሴ ሁሉ አስፈላጊውን እገዛ አጠናክሮ እንደሚቀጥል መናገራቸውን የምክር ቤቱ መረጃ ያመላክታል።

በመርሃ ግብሩ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ቴዎድሮስ ምህረት፣ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ረዳት ተጠሪ ሚኒስትር ዴኤታ መሠረት ኃይሌ፣ የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎችና አባላት፣ የተለያዩ የክልል እና የከተማ አስተዳደር የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል::

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025