የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>ምክር ቤቱ ለፌዴራል ዋና ኦዲተር የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ ይቀጥላል - ምክትል አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ሎሚ በዶ</p>

Feb 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የፌዴራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት የህዝብን ውስን ሀብት በቁጠባና ውጤታማ በሆነ መንገድ ለህዝብ አገልግሎት ተደራሽ መሆኑን የሚያረጋግጥ ተቋም እንዲሆን ምክር ቤቱ ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባዔ ወይዘሮ ሎሚ በዶ ገልፀዋል።

ምክትል አፈ ጉባኤዋ የፌዴራል ዋና ኦዲተር 80ኛ አመት የምስረታ መታሰቢያ በዓልና የሕንጻ እድሳት ምረቃ ፕሮግራም ላይ ተገኝተው መልዕክት አስተላልፈዋል።


በመልዕክታቸውም ለአንድ ሀገር እድገትና ብልጽግና በተለያዩ የስራ ዘርፎች ተሰማርተው ተልዕኳቸውን የሚወጡ የመንግስት ተቋማት የሚያበረክቱት ሁለንተናዊ አስተዋጽኦ መሠረታዊ ጉዳይ ነው ብለዋል።

በተለይም ለህብረተሰቡና ለሀገር የተለያዩ አገልግሎቶችን በማቅረብ የተጣለባቸውን ተግባርና ኃላፊነት የሚወጡ ተቋማት መንግስትና አሠራር በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት እንዲያገኙ በማድረግ ረገድ የሚጫወቱት ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ተቋማት ለህገ ወጥ አሠራር እንዳይጋለጡና በጀትና ሌሎች ግብዓቶች ለብክነት ሳይጋለጡ፤ ህግና አሠራር ተከትለው ለሚፈለገው አላማ እንዲውል እንዲሁም ብልሹ አሠራሮች እንዲታረሙና ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ የተቆጣጣሪ ተቋማትን አቅም መገንባት አስፈላጊ ነው ብለዋል።

ተቋሙ በተሰጡት ስልጣንና ተግባሮች የተቋማትን የበጀትና ንብረት አጠቃቀም እና አያያዝ ህጋዊነት ነጻና ገለልተኛ በሆነ መርህ በማረጋገጥ የተጠያቂነትና የግልጽነት አሠራር እንዲሰፍን በማድረግ የበኩሉን ሚና ሲወጣ ቆይቷል ነው ያሉት፡፡

የተለያዩ ተቋማትን አሠራር በመቆጣጠርና በመመርመር እንዲሁም የታዩ የአሠራር ችግሮችን በተለያዩ ኦዲቶች ነቅሶ በማውጣትና እንዲስተካከሉ በማድረግ የግልጽነትና የተጠያቂነት አሠራርን በማረጋገጥ ውጤታማ ስራ በማከናወን ላይ እንደሚገኝም ተናግረዋል፡፡


የተቋሙ የኦዲት አሠራር ወጥና አለም አቀፍ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ ከፌዴራል ተቋማት አልፎ ሀገራዊ እንዲሆን ለማድረግና፤ ኦዲቱ የተሻለ ደረጃ ላይ ለማድረስ የሚያስችሉትን ቅንጅታዊ አሠራሮችን በመከተል ላይ እንደሚገኝም እንስተዋል።

ምክር ቤቱ ተቋሙ ተልዕኮውን ለማሳካት በሚያደርገው እንቅስቃሴ ሁሉ አስፈላጊውን እገዛ አጠናክሮ እንደሚቀጥል መናገራቸውን የምክር ቤቱ መረጃ ያመላክታል።

በመርሃ ግብሩ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ቴዎድሮስ ምህረት፣ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ረዳት ተጠሪ ሚኒስትር ዴኤታ መሠረት ኃይሌ፣ የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎችና አባላት፣ የተለያዩ የክልል እና የከተማ አስተዳደር የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል::

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026