
አዲስ አበባ፤ የካቲት 3/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ወራት ተግባራዊ የተደረገው የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ውጤታማ ነው ሲሉ የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ ገለጹ።
የገንዘብ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የስራ አፈፃፀም ግምገማ ተካሒዷል።

ሚኒስትሩ በውይይቱ ላይ ባለፉት ስድስት ወራት ተግባራዊ የተደረገው የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ውጤታማ እንደነበር ገልጸዋል።
በቀሪው ግማሽ አመት በታክስ ፖሊሲ አፈጻጸም፣ በውጭ ሀብት አሰባሰብ፣ በዕዳ ማሸጋሸግ የጋራ ማዕቀፍ አፈጻጸሞች፣ በጥሬ ገንዘብ ፍሰት ማኔጅመንትና በበጀት ዝግጅት ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚጠበቅም ገልጸዋል።
የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ኢዮብ ተካልኝ(ዶ/ር) በበኩላቸው እንደገለጹት ያለፉት ስድስት ወራት የሥራ አፈጻጸም በተናበበና በተቀናጀ ሁኔታ የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ተግባራዊ ተደርጎ የኢኮኖሚ ማነቆ የነበሩ ችግሮች እልባት እያገኙ የመጡበት ነው ብለዋል፡፡
ይህ ተስፋ ሰጪ ውጤት ሊመዘገብ የቻለው አመራሩና ሰራተኛው ተቀናጅቶ በመስራቱ በመሆኑ ይህም ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ማሳሰባቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።
በስድስት ወራቱ የስራ አፈፃፀም ግምገማ የገንዘብ ሚኒስቴር ተጠሪ ተቋማት የሆኑት የመንግስት ግዢና ንብረት አስተዳደር ባለስልጣን፣ የመንግስት ግዢ አግልግሎትና የኢትዮጵያ ሂሳብ አያያዝና ኦዲት ቦርድ የስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም ሪፖርታቸውን አቅርበው ውይይት ተደርጎበታል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026