
አዲስ አበባ፤ የካቲት 3/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ወራት ተግባራዊ የተደረገው የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ውጤታማ ነው ሲሉ የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ ገለጹ።
የገንዘብ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የስራ አፈፃፀም ግምገማ ተካሒዷል።

ሚኒስትሩ በውይይቱ ላይ ባለፉት ስድስት ወራት ተግባራዊ የተደረገው የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ውጤታማ እንደነበር ገልጸዋል።
በቀሪው ግማሽ አመት በታክስ ፖሊሲ አፈጻጸም፣ በውጭ ሀብት አሰባሰብ፣ በዕዳ ማሸጋሸግ የጋራ ማዕቀፍ አፈጻጸሞች፣ በጥሬ ገንዘብ ፍሰት ማኔጅመንትና በበጀት ዝግጅት ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚጠበቅም ገልጸዋል።
የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ኢዮብ ተካልኝ(ዶ/ር) በበኩላቸው እንደገለጹት ያለፉት ስድስት ወራት የሥራ አፈጻጸም በተናበበና በተቀናጀ ሁኔታ የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ተግባራዊ ተደርጎ የኢኮኖሚ ማነቆ የነበሩ ችግሮች እልባት እያገኙ የመጡበት ነው ብለዋል፡፡
ይህ ተስፋ ሰጪ ውጤት ሊመዘገብ የቻለው አመራሩና ሰራተኛው ተቀናጅቶ በመስራቱ በመሆኑ ይህም ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ማሳሰባቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።
በስድስት ወራቱ የስራ አፈፃፀም ግምገማ የገንዘብ ሚኒስቴር ተጠሪ ተቋማት የሆኑት የመንግስት ግዢና ንብረት አስተዳደር ባለስልጣን፣ የመንግስት ግዢ አግልግሎትና የኢትዮጵያ ሂሳብ አያያዝና ኦዲት ቦርድ የስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም ሪፖርታቸውን አቅርበው ውይይት ተደርጎበታል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026