የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>ሳይፈቀድላቸው በአዲስ አበባና አካባቢዋ ድሮን በሚያስነሱ አካላት ላይ እርምጃ እየተወሰደ ነው - ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት</p>

Feb 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 5/2017(ኢዜአ)፦ከብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ፈቃድ ሳያገኙ በአዲስ አበባ እና አካባቢዋ ድሮን በሚያስነሱና በሚያበሩ አካላት ላይ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑ ተገለጸ።

የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት የድሮንና ሌሎች በራሪ አካላት አጠቃቀምን በተመለከተ ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ በአዲስ አበባና አካባቢዋ ማንኛውንም አይነት ድሮን ያለ አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ ፈቃድ ማስነሳትም ሆነ ማብረር እንደማይቻል በቅርቡ በመገናኛ ብዙኃን የተላለፈውን ማሳሰቢያ በማያከብሩ አካላት ላይ እርምጃ እየተወሰደ ይገኛል፡፡

በአዲስ አበባ እና አካባቢዋ ማንኛውንም አይነት ድሮን ያለ ብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ፈቃድ ማስነሳትም ሆነ ማብረር አይቻልም

በተለይ ከአፍሪካ ሕብረት ስብሰባ ጋር ተያይዞ ቅንጅታዊ ስምሪቱን ማጠናከር አስፈላጊ በመሆኑ በአዲስ አበባና አካባቢዋ ማንኛውንም አይነት ድሮን ያለ ብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት መሥሪያ ቤት ፈቃድ ማስነሳትም ሆነ ማብረር እንደማይቻል መልዕክት የተላለፈ መሆኑን ያስታወሰው መግለጫው፤ ብዙዎችም ይህን ተግባራዊ እያደረጉ መሆኑን ጠቁሟል፡፡


ማሳሰቢያውን በመጣስ ፈቃድ ሳያገኙ ድሮን ለማስነሳትና ለማብረር ሙከራ ያደረጉ አካላትን በጸረ-ድሮን ቴክኖሎጂ በመለየት ወደ ሕጋዊ አሠራር እንዲገቡ ከማድረግ ጀምሮ ተገቢው እርምጃ እየተወሰደ መሆኑንም አመልክቷል፡፡

የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት በአዋጅ በተሰጠው ስልጣን መሠረት የመሪዎችን፣ የቁልፍ መሠረተ-ልማቶችን እና ብሔራዊ ኩነቶችን ደኅንነት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን የማስጠበቅ ኃላፊነት እንዳለበት ገልጿል።

በተለይ የአፍሪካ ሕብረት ጉባዔ ስኬታማ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ድሮኖችና መሰል ቴክኖሎጂ ወለድ መሣሪያዎች የሚፈጥሯቸውን ስጋቶች ለመከላከል የሚያስችል በቂ የቴክኖሎጂ እና የሰው ኃይል ዝግጅት አድርጎ ወደ ስምሪት መግባቱን አስታውቋል፡፡


ከሥራ ጋር በተያያዘ ድሮኖችን መጠቀም የሚፈልግ ማንኛውም አካል በ+251 983 00 02 98 እና +251 983 00 04 01 ስልክ ቁጥሮች በመደወል ተጨማሪ ማብራሪያ ማግኘት እንደሚችል አገልግሎቱ አሳስቧል።

ያለፍቃድ በሚነሱ እና በሚበሩ ድሮኖች ላይ የሚደረገው ቁጥጥርና የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አመልክቷል፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025