አዳማ፤ የካቲት 5/2017(ኢዜአ)፦ የኦሮሚያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት በተያዘው ዓመት የሰብል ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያግዙ 32 ዕጩ ዝሪያዎች በምርምር ማውጣቱን ገለጸ።
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ተሾመ ቦጋለ ለኢዜአ እንደገለፁት ኢንስቲትዩቱ ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎችን በምርምር በማውጣት ለአርሶ አደሩ ተደራሽ እያደረገ ነው።
በተለይ ከክልሉ ግብርና ቢሮ ጋር በመተባበር የእርሻ ስራ ማዘመን የሚያስችሉ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽ እየተደረጉ ነው ብለዋል።
የክልሉ መንግስት በኢኒሼቲቭ መልክ እየተገበራቸው የሚገኙ የበጋ መስኖ ስንዴ፣ የቢራ ገብስ፣ የሩዝ ልማትን ጨምሮ ሌሎች የሰብል ምርትና ምርታማነትን ለማሻሻል በኢንስቲትዩቱ ተደራሽ የተደረጉ ቴክኖሎጂዎች ውጤት እያመጡ መሆኑንም ተናግረዋል።
ባለፈው ዓመት ብቻ ከ400 በላይ ግብርናን የሚያዘምኑ የምርት ማሳደጊያ ቴክኖሎጂዎችን ኢንስቲትዩቱ በምርምር ማውጣቱን ጠቅሰዋል።
በተመሳሳይ ዘንድሮም በእስከ አሁኑ ሂደት 32 ዕጩ ዝሪያዎች በምርምር ወጥተው በብሔራዊ ኮሚቴ እንዲፀድቁ ለውሳኔ ቀርበዋል ብለዋል።
ከወጡት ዕጩ ዝሪያዎች መካከል 80 በመቶ የሚሆኑት የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚያግዙ መሆናቸውን የተሻለ ምርት የሚሰጡ ስንዴ፣ ጤፍ፣ ቦቆሎ ማሽላና ጥራጥሬ ሰብል ዝርያዎች እንደሚገኙበት ተናግረዋል።
የምስራቅ ቦረና ዞን አስተዳዳሪ አቶ አብዱረዛቅ ሁሴን በዞኑ ሕዝቡ ወደ ከፊል አርብቶ አደርነት እንዲሸጋገር ለማስቻል እንዲሁም በተደጋጋሚ በአካባቢው የሚከሰተውን ድርቅ ለመቋቋም፣ የመጠጥና የመስኖ ውሃ እጥረት ለመቅረፍ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
በተለይም 'ፊና ኦሮሚያ' በተሰኘ የክልሉ መንግስት ፕሮጀክት አማካኝነት አራት ትላልቅ የመስኖና መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች በ2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር እየተገነቡ ነው ብለዋል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025