
አዳማ፤ የካቲት 5/2017(ኢዜአ)፦ የኦሮሚያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት በተያዘው ዓመት የሰብል ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያግዙ 32 ዕጩ ዝሪያዎች በምርምር ማውጣቱን ገለጸ።
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ተሾመ ቦጋለ ለኢዜአ እንደገለፁት ኢንስቲትዩቱ ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎችን በምርምር በማውጣት ለአርሶ አደሩ ተደራሽ እያደረገ ነው።
በተለይ ከክልሉ ግብርና ቢሮ ጋር በመተባበር የእርሻ ስራ ማዘመን የሚያስችሉ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽ እየተደረጉ ነው ብለዋል።
የክልሉ መንግስት በኢኒሼቲቭ መልክ እየተገበራቸው የሚገኙ የበጋ መስኖ ስንዴ፣ የቢራ ገብስ፣ የሩዝ ልማትን ጨምሮ ሌሎች የሰብል ምርትና ምርታማነትን ለማሻሻል በኢንስቲትዩቱ ተደራሽ የተደረጉ ቴክኖሎጂዎች ውጤት እያመጡ መሆኑንም ተናግረዋል።
ባለፈው ዓመት ብቻ ከ400 በላይ ግብርናን የሚያዘምኑ የምርት ማሳደጊያ ቴክኖሎጂዎችን ኢንስቲትዩቱ በምርምር ማውጣቱን ጠቅሰዋል።
በተመሳሳይ ዘንድሮም በእስከ አሁኑ ሂደት 32 ዕጩ ዝሪያዎች በምርምር ወጥተው በብሔራዊ ኮሚቴ እንዲፀድቁ ለውሳኔ ቀርበዋል ብለዋል።
ከወጡት ዕጩ ዝሪያዎች መካከል 80 በመቶ የሚሆኑት የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚያግዙ መሆናቸውን የተሻለ ምርት የሚሰጡ ስንዴ፣ ጤፍ፣ ቦቆሎ ማሽላና ጥራጥሬ ሰብል ዝርያዎች እንደሚገኙበት ተናግረዋል።
የምስራቅ ቦረና ዞን አስተዳዳሪ አቶ አብዱረዛቅ ሁሴን በዞኑ ሕዝቡ ወደ ከፊል አርብቶ አደርነት እንዲሸጋገር ለማስቻል እንዲሁም በተደጋጋሚ በአካባቢው የሚከሰተውን ድርቅ ለመቋቋም፣ የመጠጥና የመስኖ ውሃ እጥረት ለመቅረፍ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
በተለይም 'ፊና ኦሮሚያ' በተሰኘ የክልሉ መንግስት ፕሮጀክት አማካኝነት አራት ትላልቅ የመስኖና መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች በ2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር እየተገነቡ ነው ብለዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026