
አዳማ፤ የካቲት 5/2017(ኢዜአ)፦ የኦሮሚያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት በተያዘው ዓመት የሰብል ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያግዙ 32 ዕጩ ዝሪያዎች በምርምር ማውጣቱን ገለጸ።
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ተሾመ ቦጋለ ለኢዜአ እንደገለፁት ኢንስቲትዩቱ ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎችን በምርምር በማውጣት ለአርሶ አደሩ ተደራሽ እያደረገ ነው።
በተለይ ከክልሉ ግብርና ቢሮ ጋር በመተባበር የእርሻ ስራ ማዘመን የሚያስችሉ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽ እየተደረጉ ነው ብለዋል።
የክልሉ መንግስት በኢኒሼቲቭ መልክ እየተገበራቸው የሚገኙ የበጋ መስኖ ስንዴ፣ የቢራ ገብስ፣ የሩዝ ልማትን ጨምሮ ሌሎች የሰብል ምርትና ምርታማነትን ለማሻሻል በኢንስቲትዩቱ ተደራሽ የተደረጉ ቴክኖሎጂዎች ውጤት እያመጡ መሆኑንም ተናግረዋል።
ባለፈው ዓመት ብቻ ከ400 በላይ ግብርናን የሚያዘምኑ የምርት ማሳደጊያ ቴክኖሎጂዎችን ኢንስቲትዩቱ በምርምር ማውጣቱን ጠቅሰዋል።
በተመሳሳይ ዘንድሮም በእስከ አሁኑ ሂደት 32 ዕጩ ዝሪያዎች በምርምር ወጥተው በብሔራዊ ኮሚቴ እንዲፀድቁ ለውሳኔ ቀርበዋል ብለዋል።
ከወጡት ዕጩ ዝሪያዎች መካከል 80 በመቶ የሚሆኑት የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚያግዙ መሆናቸውን የተሻለ ምርት የሚሰጡ ስንዴ፣ ጤፍ፣ ቦቆሎ ማሽላና ጥራጥሬ ሰብል ዝርያዎች እንደሚገኙበት ተናግረዋል።
የምስራቅ ቦረና ዞን አስተዳዳሪ አቶ አብዱረዛቅ ሁሴን በዞኑ ሕዝቡ ወደ ከፊል አርብቶ አደርነት እንዲሸጋገር ለማስቻል እንዲሁም በተደጋጋሚ በአካባቢው የሚከሰተውን ድርቅ ለመቋቋም፣ የመጠጥና የመስኖ ውሃ እጥረት ለመቅረፍ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
በተለይም 'ፊና ኦሮሚያ' በተሰኘ የክልሉ መንግስት ፕሮጀክት አማካኝነት አራት ትላልቅ የመስኖና መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች በ2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር እየተገነቡ ነው ብለዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026