የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>ኢንስቲትዩቱ 32 ዕጩ የሰብል ዝሪያዎች በምርምር አወጣ</p>

Feb 13, 2025

IDOPRESS

አዳማ፤ የካቲት 5/2017(ኢዜአ)፦ የኦሮሚያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት በተያዘው ዓመት የሰብል ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያግዙ 32 ዕጩ ዝሪያዎች በምርምር ማውጣቱን ገለጸ።

የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ተሾመ ቦጋለ ለኢዜአ እንደገለፁት ኢንስቲትዩቱ ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎችን በምርምር በማውጣት ለአርሶ አደሩ ተደራሽ እያደረገ ነው።

በተለይ ከክልሉ ግብርና ቢሮ ጋር በመተባበር የእርሻ ስራ ማዘመን የሚያስችሉ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽ እየተደረጉ ነው ብለዋል።

የክልሉ መንግስት በኢኒሼቲቭ መልክ እየተገበራቸው የሚገኙ የበጋ መስኖ ስንዴ፣ የቢራ ገብስ፣ የሩዝ ልማትን ጨምሮ ሌሎች የሰብል ምርትና ምርታማነትን ለማሻሻል በኢንስቲትዩቱ ተደራሽ የተደረጉ ቴክኖሎጂዎች ውጤት እያመጡ መሆኑንም ተናግረዋል።

ባለፈው ዓመት ብቻ ከ400 በላይ ግብርናን የሚያዘምኑ የምርት ማሳደጊያ ቴክኖሎጂዎችን ኢንስቲትዩቱ በምርምር ማውጣቱን ጠቅሰዋል።

በተመሳሳይ ዘንድሮም በእስከ አሁኑ ሂደት 32 ዕጩ ዝሪያዎች በምርምር ወጥተው በብሔራዊ ኮሚቴ እንዲፀድቁ ለውሳኔ ቀርበዋል ብለዋል።

ከወጡት ዕጩ ዝሪያዎች መካከል 80 በመቶ የሚሆኑት የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚያግዙ መሆናቸውን የተሻለ ምርት የሚሰጡ ስንዴ፣ ጤፍ፣ ቦቆሎ ማሽላና ጥራጥሬ ሰብል ዝርያዎች እንደሚገኙበት ተናግረዋል።

የምስራቅ ቦረና ዞን አስተዳዳሪ አቶ አብዱረዛቅ ሁሴን በዞኑ ሕዝቡ ወደ ከፊል አርብቶ አደርነት እንዲሸጋገር ለማስቻል እንዲሁም በተደጋጋሚ በአካባቢው የሚከሰተውን ድርቅ ለመቋቋም፣ የመጠጥና የመስኖ ውሃ እጥረት ለመቅረፍ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በተለይም 'ፊና ኦሮሚያ' በተሰኘ የክልሉ መንግስት ፕሮጀክት አማካኝነት አራት ትላልቅ የመስኖና መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች በ2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር እየተገነቡ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026