ጎንደር፤ የካቲት 6/2017(ኢዜአ)፡- በሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ የሚገኘውን የዋልያ ዝርያ ዘላቂ ደህንነት ማስጠበቅ የሚያስችል የአስር ዓመት ስትራቴጂክ እቅድ እየተዘጋጀ መሆኑን የፓርኩ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡
የፓርኩ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ማሩ ቢያድግልኝ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የስትራቴጂክ እቅዱ ዓላማ በፓርኩ ክልል የሚፈጸሙ ህገ-ወጥ የዱር እንስሳት አደንን በማስቀረት የብርቅዬው የዋልያ ዝርያን ዘላቂ ደህንነት ለማረጋገጥ ያለመ ነው፡፡
ስትራቴጂክ እቅዱ እየተዘጋጀ የሚገኘው የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለስልጣን፣ የፍትህ፣ የግብርናና የአካባቢ ጥበቃ ተቋማት እንዲሁም ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በመተባበር መሆኑን አስረድተዋል፡፡
"ብሔራዊ የዋልያዎች ማገገሚያና መጠበቂያ" የሚል ስያሜ የተሰጠው ስትራቴጂክ እቅዱ መድረኮችን በማዘጋጀት እቅዱን ማዳበር የሚያስችሉ ግብአቶችን የማሰባሰብ ስራዎች መጀመራቸውን ጠቁመዋል፡፡
በቀጣዮቹ አስር ዓመታት ህገ-ወጥ አደንን በመቆጣጠርና አጥፊዎችን ለህግ በማቅረብ የዋልያዎችን የመኖሪያ አካባቢ ከአደጋ ስጋት ነጻ በማድረግ ቁጥራቸውን በእጥፍ ለማሳደግ እንደሚያግዝ ተናግረዋል።
በተጨማሪም የዋልያዎችን የጤናና የውልደት ምጣኔ ለማሻሻል የሚያግዙ ሳይንሳዊ ምርምሮችን ማካሄድና የህብረተሰቡን የግንዛቤ ደረጃ ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እንደሚከናወኑ ገልጸዋል፡፡
እቅዱን ዘንድሮ በማጠናቀቅ በቀጣዩ ዓመት በብሔራዊ ደረጃ በሚመለከተው አካል በማጸደቅ ወደ ትግበራ እንደሚሸጋገር ጠቁመዋል።
እንደ አውሮፓ አቆጣጠር በ1978 በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት/ዩኔስኮ/ በአለም የተፈጥሮ ቅርስነት የተመዘገበው የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ 412 ስኩየር ኪሎ ሜትር ስፋት የሚሸፍን መሆኑ ተመልክቷል፡፡
በፓርኩ ውስጥም በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙ ዋልያ፤ ቀይ ቀበሮና ጭላዳ ዝንጀሮን ጨምሮ ሌሎች ብርቅዬ የዱር እንስሳትና አእዋፋት መገኛ መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025