የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>የዋልያ ዝርያን ዘላቂ ደህንነት ማስጠበቅ የሚያስችል ስትራቴጂክ እቅድ እየተዘጋጀ ነው</p>

Feb 13, 2025

IDOPRESS

ጎንደር፤ የካቲት 6/2017(ኢዜአ)፡- በሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ የሚገኘውን የዋልያ ዝርያ ዘላቂ ደህንነት ማስጠበቅ የሚያስችል የአስር ዓመት ስትራቴጂክ እቅድ እየተዘጋጀ መሆኑን የፓርኩ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡


የፓርኩ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ማሩ ቢያድግልኝ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የስትራቴጂክ እቅዱ ዓላማ በፓርኩ ክልል የሚፈጸሙ ህገ-ወጥ የዱር እንስሳት አደንን በማስቀረት የብርቅዬው የዋልያ ዝርያን ዘላቂ ደህንነት ለማረጋገጥ ያለመ ነው፡፡


ስትራቴጂክ እቅዱ እየተዘጋጀ የሚገኘው የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለስልጣን፣ የፍትህ፣ የግብርናና የአካባቢ ጥበቃ ተቋማት እንዲሁም ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በመተባበር መሆኑን አስረድተዋል፡፡


"ብሔራዊ የዋልያዎች ማገገሚያና መጠበቂያ" የሚል ስያሜ የተሰጠው ስትራቴጂክ እቅዱ መድረኮችን በማዘጋጀት እቅዱን ማዳበር የሚያስችሉ ግብአቶችን የማሰባሰብ ስራዎች መጀመራቸውን ጠቁመዋል፡፡


በቀጣዮቹ አስር ዓመታት ህገ-ወጥ አደንን በመቆጣጠርና አጥፊዎችን ለህግ በማቅረብ የዋልያዎችን የመኖሪያ አካባቢ ከአደጋ ስጋት ነጻ በማድረግ ቁጥራቸውን በእጥፍ ለማሳደግ እንደሚያግዝ ተናግረዋል።


በተጨማሪም የዋልያዎችን የጤናና የውልደት ምጣኔ ለማሻሻል የሚያግዙ ሳይንሳዊ ምርምሮችን ማካሄድና የህብረተሰቡን የግንዛቤ ደረጃ ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እንደሚከናወኑ ገልጸዋል፡፡


እቅዱን ዘንድሮ በማጠናቀቅ በቀጣዩ ዓመት በብሔራዊ ደረጃ በሚመለከተው አካል በማጸደቅ ወደ ትግበራ እንደሚሸጋገር ጠቁመዋል።


እንደ አውሮፓ አቆጣጠር በ1978 በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት/ዩኔስኮ/ በአለም የተፈጥሮ ቅርስነት የተመዘገበው የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ 412 ስኩየር ኪሎ ሜትር ስፋት የሚሸፍን መሆኑ ተመልክቷል፡፡


በፓርኩ ውስጥም በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙ ዋልያ፤ ቀይ ቀበሮና ጭላዳ ዝንጀሮን ጨምሮ ሌሎች ብርቅዬ የዱር እንስሳትና አእዋፋት መገኛ መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው &quot;ቡኖ - ማላ&quot; ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026