
ጎንደር፤ የካቲት 6/2017(ኢዜአ)፡- በሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ የሚገኘውን የዋልያ ዝርያ ዘላቂ ደህንነት ማስጠበቅ የሚያስችል የአስር ዓመት ስትራቴጂክ እቅድ እየተዘጋጀ መሆኑን የፓርኩ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡
የፓርኩ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ማሩ ቢያድግልኝ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የስትራቴጂክ እቅዱ ዓላማ በፓርኩ ክልል የሚፈጸሙ ህገ-ወጥ የዱር እንስሳት አደንን በማስቀረት የብርቅዬው የዋልያ ዝርያን ዘላቂ ደህንነት ለማረጋገጥ ያለመ ነው፡፡
ስትራቴጂክ እቅዱ እየተዘጋጀ የሚገኘው የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለስልጣን፣ የፍትህ፣ የግብርናና የአካባቢ ጥበቃ ተቋማት እንዲሁም ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በመተባበር መሆኑን አስረድተዋል፡፡
"ብሔራዊ የዋልያዎች ማገገሚያና መጠበቂያ" የሚል ስያሜ የተሰጠው ስትራቴጂክ እቅዱ መድረኮችን በማዘጋጀት እቅዱን ማዳበር የሚያስችሉ ግብአቶችን የማሰባሰብ ስራዎች መጀመራቸውን ጠቁመዋል፡፡
በቀጣዮቹ አስር ዓመታት ህገ-ወጥ አደንን በመቆጣጠርና አጥፊዎችን ለህግ በማቅረብ የዋልያዎችን የመኖሪያ አካባቢ ከአደጋ ስጋት ነጻ በማድረግ ቁጥራቸውን በእጥፍ ለማሳደግ እንደሚያግዝ ተናግረዋል።
በተጨማሪም የዋልያዎችን የጤናና የውልደት ምጣኔ ለማሻሻል የሚያግዙ ሳይንሳዊ ምርምሮችን ማካሄድና የህብረተሰቡን የግንዛቤ ደረጃ ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እንደሚከናወኑ ገልጸዋል፡፡
እቅዱን ዘንድሮ በማጠናቀቅ በቀጣዩ ዓመት በብሔራዊ ደረጃ በሚመለከተው አካል በማጸደቅ ወደ ትግበራ እንደሚሸጋገር ጠቁመዋል።
እንደ አውሮፓ አቆጣጠር በ1978 በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት/ዩኔስኮ/ በአለም የተፈጥሮ ቅርስነት የተመዘገበው የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ 412 ስኩየር ኪሎ ሜትር ስፋት የሚሸፍን መሆኑ ተመልክቷል፡፡
በፓርኩ ውስጥም በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙ ዋልያ፤ ቀይ ቀበሮና ጭላዳ ዝንጀሮን ጨምሮ ሌሎች ብርቅዬ የዱር እንስሳትና አእዋፋት መገኛ መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026