ጋምቤላ፤ የካቲት 6/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በመጪው የመኸር እርሻ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፈር ማዳበሪያ በመጠቀም ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ አስታወቀ።
በምርት ዘመኑ ከ172 ሺህ 230 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑንም ቢሮው ገልጿል።
በጋምቤላ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ የእርሻ ዘርፍ ምክትል ኃላፊ አቶ ዳግም ምላሽን ለኢዜአ እንደገለጹት በክልሉ በ2017/18 የምርት ዘመን ለመጀመሪያ ጊዜ የአፈር ማዳበሪያን ጨምሮ ሌሎች ሙሉ የምርት ማሳደጊያ ግብዓቶችን በመጠቀም ምርታማነትን ለማሳደግ ታቅዶ ወደ ሥራ ተገብቷል።
ከአሁን በፊት ለክልሉ አርሶና ከፊል አርብቶ አደሮች የምርት ማሳዳጊያ ግብዓት በተሟላ መልኩ አለመቅረቡ በምርት እድገቱ ላይ ተጽዕኖ ፈጥሮ መቆየቱን ጠቁመው፤ በዘንድሮው የምርት ዘመን የግብዓት ችግሮችን ለመፍታት እንደሚሰራ ተናግረዋል።
በተለይም ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ግብርናውን በቴክኖሎጂ መደገፍ አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል።
በተለይም በዘንድሮው የመኸር እርሻ በክልሉ የአፈር ማዳበሪያን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ በማዋል ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል ብለዋል።
በአሁኑ ወቅት ወደ ክልሉ 60 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ መግባቱን ጠቁመው፤ የአርሶና ከፊል አርብቶ አደሮች እንዲሁም የባለሃብቶች ፍላጎት እየታየ የግብዓት አቅርቦቱ እንደሚጨምር አስረድተዋል።
በምርት ዘመኑ በክልሉ ከ172 ሺህ 230 ሄክታር በላይ መሬት በማልማት ከ5 ነጥብ 2 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ግብ ተጥሎ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
አሁን ላይ እቅዱን ለማሳካት ከማዳበሪያ ግብዓት አቅርቦት በተጨማሪ ከ5 ሺህ ኩንታል በላይ የበቆሎ፣ የማሽላ፣ የሩዝና ሌሎች የምርጥ ዘር ግብዓትና የእርሻ ትራክተር ለማቅረብ እየተሰራ ነው ብለዋል።
በክልሉ በመጪው የመኸር እርሻ ለማልማት የታቀደው መሬት ካለፈው ዓመት በስድስት ሺህ ሄክታር፤ በምርት መጠን ደግሞ ከ400 ሺህ ኩንታል በላይ ብልጫ ያለው እንደሆነ ምክትል ቢሮ ኃላፊው አመላክተዋል።
በቢሮው የምርት ግብዓት አቅርቦት ዳይሬክተር አባላ ኡቦንግ(ዶ/ር) በበኩላቸው ግብዓት መቅረቡ ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የታለመውን ግብ ለማሳካት የጎላ ፋይዳ ይኖረዋል ብለዋል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025