የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>በጋምቤላ ክልል ለመጀመሪያ ጊዜ የአፈር ማዳበሪያ በመጠቀም ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ ነው - ቢሮው</p>

Feb 14, 2025

IDOPRESS

ጋምቤላ፤ የካቲት 6/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በመጪው የመኸር እርሻ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፈር ማዳበሪያ በመጠቀም ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ አስታወቀ።

በምርት ዘመኑ ከ172 ሺህ 230 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑንም ቢሮው ገልጿል።

በጋምቤላ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ የእርሻ ዘርፍ ምክትል ኃላፊ አቶ ዳግም ምላሽን ለኢዜአ እንደገለጹት በክልሉ በ2017/18 የምርት ዘመን ለመጀመሪያ ጊዜ የአፈር ማዳበሪያን ጨምሮ ሌሎች ሙሉ የምርት ማሳደጊያ ግብዓቶችን በመጠቀም ምርታማነትን ለማሳደግ ታቅዶ ወደ ሥራ ተገብቷል።

ከአሁን በፊት ለክልሉ አርሶና ከፊል አርብቶ አደሮች የምርት ማሳዳጊያ ግብዓት በተሟላ መልኩ አለመቅረቡ በምርት እድገቱ ላይ ተጽዕኖ ፈጥሮ መቆየቱን ጠቁመው፤ በዘንድሮው የምርት ዘመን የግብዓት ችግሮችን ለመፍታት እንደሚሰራ ተናግረዋል።

በተለይም ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ግብርናውን በቴክኖሎጂ መደገፍ አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል።

በተለይም በዘንድሮው የመኸር እርሻ በክልሉ የአፈር ማዳበሪያን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ በማዋል ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል ብለዋል።

በአሁኑ ወቅት ወደ ክልሉ 60 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ መግባቱን ጠቁመው፤ የአርሶና ከፊል አርብቶ አደሮች እንዲሁም የባለሃብቶች ፍላጎት እየታየ የግብዓት አቅርቦቱ እንደሚጨምር አስረድተዋል።

በምርት ዘመኑ በክልሉ ከ172 ሺህ 230 ሄክታር በላይ መሬት በማልማት ከ5 ነጥብ 2 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ግብ ተጥሎ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።

አሁን ላይ እቅዱን ለማሳካት ከማዳበሪያ ግብዓት አቅርቦት በተጨማሪ ከ5 ሺህ ኩንታል በላይ የበቆሎ፣ የማሽላ፣ የሩዝና ሌሎች የምርጥ ዘር ግብዓትና የእርሻ ትራክተር ለማቅረብ እየተሰራ ነው ብለዋል።

በክልሉ በመጪው የመኸር እርሻ ለማልማት የታቀደው መሬት ካለፈው ዓመት በስድስት ሺህ ሄክታር፤ በምርት መጠን ደግሞ ከ400 ሺህ ኩንታል በላይ ብልጫ ያለው እንደሆነ ምክትል ቢሮ ኃላፊው አመላክተዋል።


በቢሮው የምርት ግብዓት አቅርቦት ዳይሬክተር አባላ ኡቦንግ(ዶ/ር) በበኩላቸው ግብዓት መቅረቡ ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የታለመውን ግብ ለማሳካት የጎላ ፋይዳ ይኖረዋል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026