
ጋምቤላ፤ የካቲት 6/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በመጪው የመኸር እርሻ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፈር ማዳበሪያ በመጠቀም ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ አስታወቀ።
በምርት ዘመኑ ከ172 ሺህ 230 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑንም ቢሮው ገልጿል።
በጋምቤላ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ የእርሻ ዘርፍ ምክትል ኃላፊ አቶ ዳግም ምላሽን ለኢዜአ እንደገለጹት በክልሉ በ2017/18 የምርት ዘመን ለመጀመሪያ ጊዜ የአፈር ማዳበሪያን ጨምሮ ሌሎች ሙሉ የምርት ማሳደጊያ ግብዓቶችን በመጠቀም ምርታማነትን ለማሳደግ ታቅዶ ወደ ሥራ ተገብቷል።
ከአሁን በፊት ለክልሉ አርሶና ከፊል አርብቶ አደሮች የምርት ማሳዳጊያ ግብዓት በተሟላ መልኩ አለመቅረቡ በምርት እድገቱ ላይ ተጽዕኖ ፈጥሮ መቆየቱን ጠቁመው፤ በዘንድሮው የምርት ዘመን የግብዓት ችግሮችን ለመፍታት እንደሚሰራ ተናግረዋል።
በተለይም ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ግብርናውን በቴክኖሎጂ መደገፍ አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል።
በተለይም በዘንድሮው የመኸር እርሻ በክልሉ የአፈር ማዳበሪያን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ በማዋል ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል ብለዋል።
በአሁኑ ወቅት ወደ ክልሉ 60 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ መግባቱን ጠቁመው፤ የአርሶና ከፊል አርብቶ አደሮች እንዲሁም የባለሃብቶች ፍላጎት እየታየ የግብዓት አቅርቦቱ እንደሚጨምር አስረድተዋል።
በምርት ዘመኑ በክልሉ ከ172 ሺህ 230 ሄክታር በላይ መሬት በማልማት ከ5 ነጥብ 2 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ግብ ተጥሎ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
አሁን ላይ እቅዱን ለማሳካት ከማዳበሪያ ግብዓት አቅርቦት በተጨማሪ ከ5 ሺህ ኩንታል በላይ የበቆሎ፣ የማሽላ፣ የሩዝና ሌሎች የምርጥ ዘር ግብዓትና የእርሻ ትራክተር ለማቅረብ እየተሰራ ነው ብለዋል።
በክልሉ በመጪው የመኸር እርሻ ለማልማት የታቀደው መሬት ካለፈው ዓመት በስድስት ሺህ ሄክታር፤ በምርት መጠን ደግሞ ከ400 ሺህ ኩንታል በላይ ብልጫ ያለው እንደሆነ ምክትል ቢሮ ኃላፊው አመላክተዋል።

በቢሮው የምርት ግብዓት አቅርቦት ዳይሬክተር አባላ ኡቦንግ(ዶ/ር) በበኩላቸው ግብዓት መቅረቡ ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የታለመውን ግብ ለማሳካት የጎላ ፋይዳ ይኖረዋል ብለዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026