የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>በጋምቤላ ክልል ለመጀመሪያ ጊዜ የአፈር ማዳበሪያ በመጠቀም ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ ነው - ቢሮው</p>

Feb 14, 2025

IDOPRESS

ጋምቤላ፤ የካቲት 6/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በመጪው የመኸር እርሻ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፈር ማዳበሪያ በመጠቀም ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ አስታወቀ።

በምርት ዘመኑ ከ172 ሺህ 230 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑንም ቢሮው ገልጿል።

በጋምቤላ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ የእርሻ ዘርፍ ምክትል ኃላፊ አቶ ዳግም ምላሽን ለኢዜአ እንደገለጹት በክልሉ በ2017/18 የምርት ዘመን ለመጀመሪያ ጊዜ የአፈር ማዳበሪያን ጨምሮ ሌሎች ሙሉ የምርት ማሳደጊያ ግብዓቶችን በመጠቀም ምርታማነትን ለማሳደግ ታቅዶ ወደ ሥራ ተገብቷል።

ከአሁን በፊት ለክልሉ አርሶና ከፊል አርብቶ አደሮች የምርት ማሳዳጊያ ግብዓት በተሟላ መልኩ አለመቅረቡ በምርት እድገቱ ላይ ተጽዕኖ ፈጥሮ መቆየቱን ጠቁመው፤ በዘንድሮው የምርት ዘመን የግብዓት ችግሮችን ለመፍታት እንደሚሰራ ተናግረዋል።

በተለይም ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ግብርናውን በቴክኖሎጂ መደገፍ አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል።

በተለይም በዘንድሮው የመኸር እርሻ በክልሉ የአፈር ማዳበሪያን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ በማዋል ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል ብለዋል።

በአሁኑ ወቅት ወደ ክልሉ 60 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ መግባቱን ጠቁመው፤ የአርሶና ከፊል አርብቶ አደሮች እንዲሁም የባለሃብቶች ፍላጎት እየታየ የግብዓት አቅርቦቱ እንደሚጨምር አስረድተዋል።

በምርት ዘመኑ በክልሉ ከ172 ሺህ 230 ሄክታር በላይ መሬት በማልማት ከ5 ነጥብ 2 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ግብ ተጥሎ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።

አሁን ላይ እቅዱን ለማሳካት ከማዳበሪያ ግብዓት አቅርቦት በተጨማሪ ከ5 ሺህ ኩንታል በላይ የበቆሎ፣ የማሽላ፣ የሩዝና ሌሎች የምርጥ ዘር ግብዓትና የእርሻ ትራክተር ለማቅረብ እየተሰራ ነው ብለዋል።

በክልሉ በመጪው የመኸር እርሻ ለማልማት የታቀደው መሬት ካለፈው ዓመት በስድስት ሺህ ሄክታር፤ በምርት መጠን ደግሞ ከ400 ሺህ ኩንታል በላይ ብልጫ ያለው እንደሆነ ምክትል ቢሮ ኃላፊው አመላክተዋል።


በቢሮው የምርት ግብዓት አቅርቦት ዳይሬክተር አባላ ኡቦንግ(ዶ/ር) በበኩላቸው ግብዓት መቅረቡ ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የታለመውን ግብ ለማሳካት የጎላ ፋይዳ ይኖረዋል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026