
አዲስ አበባ፤የካቲት 9/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያን ምርት በአፍሪካ ገበያ በብዛት እንዲቀርብ እየሰራ መሆኑን የአፍሪካ ኤሌክትሮኒክ ንግድ ግሩፕ ገለጸ፡፡
የአፍሪካ ኤሌክትሮኒክ ንግድ ግሩፕ ዋና ሃላፊ ሙሉአለም ስዩም ለኢዜአ እንደገለጹት፥ ግሩፑ ከአፍሪካ ህብረት ጋር ስትራቴጂክ አጋር በመሆን እየሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡
የአፍሪካ ኤሌክትሮኒክ ንግድ ግሩፕ የአህጉሪቱ አነስተኛ እና መካከለኛ ስራ ፈጣሪዎች በአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጠና እንዲሰሩ የሚያስችል ኢንሼቲቭ ይዞ እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡
ግሩፑ ሶኮኩ አፍሪካ የተባለ በበይነ መረብ የሚከናወን አህጉር አቀፍ ገበያ በማቅረብም የአፍሪካ ምርቶችን ብቻ የማስተዋወቅና የገበያ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ በመስራት ላይ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
በሌላ መልኩም የአፍሪካ ኤሌክትሮኒክ ንግድ ግሩፕ ሁሉን ያማከለ የፋይናንስ ስርዓት እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ላይ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በሶኮኩ አፍሪካ በርካታ የአነስተኛ የንግድ ባለቤቶች ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቅሰው፥ ከኢትዮጵያም በርካታ አነስተኛና መካከለኛ ስራ ፈጣሪዎች የገበያ ዕድል ማግኘታቸውን ገልጸዋል፡፡
ግሩፑ ተቀማጭነቱን አዲስ አበባ ማድረጉን ጠቁመው፤ ከኢትዮጵያ የግል ዘርፍ እና ከሌሎችም ጋር በትብብር በመስራት የኢትዮጵያን ምርት ለአፍሪካ ገበያ ለማቅረብ እየሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
ባለፉት ሁለት ዓመታት በአህጉር አቀፍ ደረጃ ወደ 170 ሺህ የሚጠጉ ቢዝነሶች በበይነ መረቡ በመገበያየት ላይ እንደሚገኙም ተናግረዋል፡፡
ከአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ጋር በመተባበርም በበርካታ አህጉር አቀፍ ደረጃም ሌሎች ቢዝነሶች ወደ ግብይት እንዲገቡ እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
ግሩፑ ለወጣቶች የስራ ዕድል ፈጠራ ትኩረቱን አድርጎ እንደሚሰራ ጠቁመው፥ ቢዝነሶችን በማሳደግ፣ምርቶችን እንዲያስተዋውቁና የገበያ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026