
አዲስ አበባ፤የካቲት 9/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የንግድ ሥርዓት ውስጥ መግባቷን ለማረጋገጥ ቁርጠኞች ነን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከዓለም ንግድ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ከሆኑት ንጎዚ ኦኮንጆ ጋር ተወያይተዋል።
በውይይታቸውም፥ኢትዮጵያ የአለም ንግድ ድርጅት አባል በመሆን ሂደት ውስጥ አመታትን ማስቆጠሯን ገልጸዋል።
የአባልነት ሂደቱን ለማሳካትም በቀጣይ ሊደረጉ ሊወሰዱ በሚገባቸው እርምጃዎች ላይ መወያየታቸውን በኤክስ ገጻቸው አስፍረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ በቀጣይ ሊደረጉ የሚገባቸው አስፈላጊ መስፈርቶች በመጠናቀቅ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የአለም ንግድ ድርጅት አባልነትን ከብሄራዊ ጥቅማችን ጋር በማስተሳሰር ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የንግድ ሥርዓት ውስጥ መግባቷን ለማረጋገጥ ቁርጠኞች ነን ብለዋል።
አክለውም፥ የአለም ንግድ ድርጅት አባልነቱን ለማፋጠን፥ ኢትዮጵያ በአገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም እያስመዘገበች ያለው እድገት ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026