የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

<p>ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የንግድ ሥርዓት ውስጥ መግባቷን ለማረጋገጥ ቁርጠኞች ነን- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)</p>

Feb 17, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤የካቲት 9/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የንግድ ሥርዓት ውስጥ መግባቷን ለማረጋገጥ ቁርጠኞች ነን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከዓለም ንግድ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ከሆኑት ንጎዚ ኦኮንጆ ጋር ተወያይተዋል።

በውይይታቸውም፥ኢትዮጵያ የአለም ንግድ ድርጅት አባል በመሆን ሂደት ውስጥ አመታትን ማስቆጠሯን ገልጸዋል።

የአባልነት ሂደቱን ለማሳካትም በቀጣይ ሊደረጉ ሊወሰዱ በሚገባቸው እርምጃዎች ላይ መወያየታቸውን በኤክስ ገጻቸው አስፍረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ በቀጣይ ሊደረጉ የሚገባቸው አስፈላጊ መስፈርቶች በመጠናቀቅ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የአለም ንግድ ድርጅት አባልነትን ከብሄራዊ ጥቅማችን ጋር በማስተሳሰር ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የንግድ ሥርዓት ውስጥ መግባቷን ለማረጋገጥ ቁርጠኞች ነን ብለዋል።

አክለውም፥ የአለም ንግድ ድርጅት አባልነቱን ለማፋጠን፥ ኢትዮጵያ በአገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም እያስመዘገበች ያለው እድገት ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025