
አዲስ አበባ፤የካቲት 9/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የንግድ ሥርዓት ውስጥ መግባቷን ለማረጋገጥ ቁርጠኞች ነን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከዓለም ንግድ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ከሆኑት ንጎዚ ኦኮንጆ ጋር ተወያይተዋል።
በውይይታቸውም፥ኢትዮጵያ የአለም ንግድ ድርጅት አባል በመሆን ሂደት ውስጥ አመታትን ማስቆጠሯን ገልጸዋል።
የአባልነት ሂደቱን ለማሳካትም በቀጣይ ሊደረጉ ሊወሰዱ በሚገባቸው እርምጃዎች ላይ መወያየታቸውን በኤክስ ገጻቸው አስፍረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ በቀጣይ ሊደረጉ የሚገባቸው አስፈላጊ መስፈርቶች በመጠናቀቅ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የአለም ንግድ ድርጅት አባልነትን ከብሄራዊ ጥቅማችን ጋር በማስተሳሰር ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የንግድ ሥርዓት ውስጥ መግባቷን ለማረጋገጥ ቁርጠኞች ነን ብለዋል።
አክለውም፥ የአለም ንግድ ድርጅት አባልነቱን ለማፋጠን፥ ኢትዮጵያ በአገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም እያስመዘገበች ያለው እድገት ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026