
አዲስ አበባ፤የካቲት 9/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የንግድ ሥርዓት ውስጥ መግባቷን ለማረጋገጥ ቁርጠኞች ነን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከዓለም ንግድ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ከሆኑት ንጎዚ ኦኮንጆ ጋር ተወያይተዋል።
በውይይታቸውም፥ኢትዮጵያ የአለም ንግድ ድርጅት አባል በመሆን ሂደት ውስጥ አመታትን ማስቆጠሯን ገልጸዋል።
የአባልነት ሂደቱን ለማሳካትም በቀጣይ ሊደረጉ ሊወሰዱ በሚገባቸው እርምጃዎች ላይ መወያየታቸውን በኤክስ ገጻቸው አስፍረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ በቀጣይ ሊደረጉ የሚገባቸው አስፈላጊ መስፈርቶች በመጠናቀቅ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የአለም ንግድ ድርጅት አባልነትን ከብሄራዊ ጥቅማችን ጋር በማስተሳሰር ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የንግድ ሥርዓት ውስጥ መግባቷን ለማረጋገጥ ቁርጠኞች ነን ብለዋል።
አክለውም፥ የአለም ንግድ ድርጅት አባልነቱን ለማፋጠን፥ ኢትዮጵያ በአገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም እያስመዘገበች ያለው እድገት ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026