የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>የአህጉሪቱን ዕድገት የሚያፋጥኑ ከ70 በላይ ታላላቅ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ ነው - የአፍሪካ ህብረት የመሰረተ ልማትና ኢነርጂ ኮሚሽን</p>

Feb 17, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 9/2017(ኢዜአ)፡- የአፍሪካን ዕድገት የሚያፋጥኑ ከ70 በላይ ታላላቅ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ እንደሚገኙ የአፍሪካ ህብረት የመሰረተ ልማትና ኢነርጂ ኮሚሽን ገለጸ።

ተሰናባቿ የአፍሪካ ህብረት የመሰረተ ልማትና ኢነርጂ ኮሚሽን ኮሚሽነር አማኒ አቡዜይድ በአፍሪካ እየተከናወኑ የሚገኙ ግዙፍ የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን አስመልክተው ለመገናኛ ብዙሃን ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በማብራሪያቸውም፥ በአህጉሪቱ እ.አ.አ ከ2021 ጀምሮ ከ70 በላይ ዕድገትን የሚያፋጥኑ ታላላቅ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ እንደሚገኙ አስታውቀዋል።

አህጉሪቱ አንድ የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት እንዲኖራት የሚደረገው ጥረት በአፍሪካ ከሚከናወኑ ግዙፍ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ መሆኑንም አስረድተዋል።

በ2023 ይፋ የተደረገውን የአንድ አፍሪካ አየር ትራንስፖርት መርኃ ግብር ተከትሎ 39 የአህጉሪቱ ሀገራት መርኃ ግብሩን መቀላቀላቸውን አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአህጉሪቱን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስር በማሳለጥ በአየር ትራንስፖርት ዘርፍ ገንቢ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ አብራርተዋል።

በ2017 የተጀመረውን የታዳሽ ኃይል አቅርቦት መርኃ ግብር መነሻ በማድረግ አህጉሪቱ በታዳሽ ኃይል ልማት ተጠቃሚ እንድትሆን እየተሰራ እንደሚገኝም ገልጸዋል።

በአፍሪካ በቂ የኃይል አቅርቦት ባለመኖሩ የታዳሽ ኃይል አቅርቦት ልማት መርኃ ግብሩ ችግሩን ለመፍታት ገንቢ ሚና እንደሚኖረው ተናግረዋል።

በታዳሽ ኃይል አቅርቦት መርኃ ግብር ከአየር ንብረት ተጽዕኖ የጸዳ ሃይል ተደራሽ ማድረግ የሚያስችል ስራ እየተሰራ መሆኑንም አስረድተዋል።

በ2021 የተጀመረው የአፍሪካ ዲጂታል ስትራቴጂ አፍሪካ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚያደርጋትን ዳታ እንድታመነጭ እና ከሳይበር ጥቃት ራሷን እንድትከላከል ያለመ እንደሆነም አንስተዋል።

አፍሪካን እርስ በእርስ የሚያስተሳስረው የባቡር መሥመር ዝርጋታ በአህጉሪቱ ከሚከናወኑ ግዙፍ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች አንዱ መሆኑን ገልጸዋል።

ሰው ሰራሽ አስተውሎትን በተመለከተ የአፍሪካን ተወዳዳሪነት የሚያሳድግ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝም አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው &quot;ቡኖ - ማላ&quot; ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026