የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>የኢንዱስትሪዎችን ተወዳዳሪነት የሚያሳድጉና በቴክኖሎጂ የተደገፉ የምርምር ውጤቶች ተግባር ላይ እንዲውሉ እየተሰራ ነው</p>

Feb 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤የካቲት 10/2017(ኢዜአ)፦የኢንዱስትሪዎችን ተወዳዳሪነት የሚያሳድጉና በቴክኖሎጂ የተደገፉ የምርምር ውጤቶች ተግባር ላይ እንዲውሉ በትኩረት እየሰራ መሆኑን የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ አስታወቀ፡፡

የቴክኖሎጂ ምርምር ውጤቶች ወደ ተግባር ተለውጠው ለኢትዮጵያ ኢንዱስትሪና ኢኮኖሚ አድገት እንዲውሉ በትኩረት እየሰራ መሆኑን የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ አስታውቋል፡፡


በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት ዘጠነኛው ዓለም አቀፍ የምርምር ጉባኤ "ሳይንስ ቴክኖሎጂ ኢኖቬሽን ለኢንዱስትሪ" በሚል መሪ ሃሳብ መካሄድ ጀምሯል፡፡

የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ደረጄ እንግዳ በወቅቱ እንደገለጹት፥ ዓለም አንድ በሆነችበት በዚህ ዘመን እድገትና ልማትን ያለ ቴክኖሎጂና ሳይንስ ማሰብ አይቻልም፡፡

ኢትዮጵያ በሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንቨስት ማድረጓ በምግብ ራሷን ለመቻል፣ዘላቂ የሃይል አቅርቦትን ለማረጋገጥ ፣ የጤና ስርአቱን ለማሻሻልና ኢንዱስትሪውን ለማዘመን ወሳኝ ጉዳይ መሆናቸውን አመልክተዋል፡፡

ዩኒቨርስቲው የቴክኖሎጂ ምርምሮች ወደ ተግባር ተለውጠው የአገሪቱን ኢኮኖሚ እና እድገት እንዲያፋጥኑ ከተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማትና አጋር አካላት ጋር እየሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡

ዩኒቨርስቲው የተለያዩ የቴክኖሎጂ የፈጠራ ውጤቶችንና በዘርፉ የሰለጠነ የሰው ሃይል በማውጣት ኢንዱስትሪዎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ሚናውን እየተወጣ ይገኛል ብለዋል፡፡

የዩኒቨርሲቲው የምርምር እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር አብርሃም ደበበ በበኩላቸው፥ ዩንቨርስቲው ስድስት የልህቀት ማዕከል በመገንባት በሳይንስና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በርካታ ተግባራት እያከናወነ እንደሚገኝ አንስተዋል፡፡

ዩኒቨርሲቲው ከኢንዱስትሪዎች ጋር በመተባበር የሚያከናውናቸው ተግባራት ውጤት እያሳዩ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

በኢትዮጵያ የኦስትሪያ አምባሳደር ዶክተር ሲሞን ናብ የሳይንስና የቴክኖሎጂ የፈጠራ ውጤቶች ለአንድ አገር ሁለንተናዊ እድገት ወሳኝ በመሆናቸው በትኩረት መስራት ይገባል ብለዋል፡፡

የኦስትሪያ ዩንቨርስቲዎች ከኢትየጵያ ዩኒቨርስቲዎች ጋር በጉዳዩ ላይ በጋራ በርካታ ተግባራት እያከናወኑ ሲሆን በቀጣይም የሚሰሩት ስራ በተጠናከረ ሁኔታ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡

አዲስ አበባን ዘመናዊና ስማርት ሲቲ በማድረግ ሂደት ዩኒቨርስቲው ወሳኝ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ የገለጹት ደግሞ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ምክትል ቢሮ ሃላፊ ዶክተር ቱሉ ጥላሁን ናቸው፡፡

በከተማዋ በሚሰሩ የቴክኖሎጂ ልማት ስራዎች ከዩኒቨርስቲው ጋር በትብብር መስራታቸውን እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው &quot;ቡኖ - ማላ&quot; ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026