
መቀሌ፤ የካቲት 10/2017(ኢዜአ)፡- በትግራይ ክልል ዘላቂ ሰላምን በማስፈንና እምቅ የሆነውን የተፈጥሮ ሃብት በማልማት የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ተገልጿል።
የክልሉ ኢኮኖሚ ያለበትን ሁኔታ እና ማተኮር በሚገቡ አቅጣጫዎችን የተመለከተ ፎረም በመቀሌ ተካሂዷል።
በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የፖሊሲ ጥናትና ምርምር ኢንስቲትዩት ከፍተኛ ተመራማሪ ካህሳይ በርሄ(ዶ/ር) የውይይት መነሻ ፅሑፍ ባቀረቡበት ወቅት እንዳሉት፤ የክልሉን ኢንቨስትመንት እና ኢኮኖሚ ለማሳደግ ምቹ ሁኔታን መፍጠር እና ሰላምን ማጠናከር ይገባል።

ክልሉ የበርካታ ፀጋዎች ባለቤት መሆኑን ጠቁመው በተለይ በግብርና፣ በማዕድንና በቱሪዝም ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን በአግባቡ ጥቅም ላይ ለማዋል ሰላምና መረጋጋትን ማጠናከር ወሳኝ ነው ብለዋል።
በአጠቃላይ የክልሉን ኢኮኖሚ ለማሳደግ የሲቪል ሰርቫንቱን ጨምሮ የአሰራርና የተቋማት ሪፎርም ትግበራዎችን ማከናወን አስፈላጊ እንደሆነም ጨምረው አመላክተዋል።
በኢንስቲትዩቱ የኢኮኖሚ ምሁር አርዓያ መብራህቱ(ዶ/ር) በበኩላቸው የክልሉን ኢኮኖሚ ለማሳደግ የግብርና፣ የኢንዱስትሪ እና የአገልግሎት ዘርፎች ትኩረት ሊሰጣቸው ይገባል ብለዋል።
በፌዴራል መንግስት እየተደረጉ ያሉ ድጋፎች መጠናከር ወሳኝ መሆኑን አንስተው የክልሉን እምቅ ሃብት የማልማትና የመጠቀም ስራ ሊጠናከር ይገባል ነው ያሉት።
የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ለማስቀጠልና የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከምንም በላይ የክልሉን ሰላም ለማፅናት በትብብርና በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባም ተናግረዋል።
በክልሉ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም፣ የማህበራዊ ትስስርና የአስተሳሰብ ለውጥ ማምጣት አለብን ያሉት ደግሞ በጊዜያዊ አስተዳደሩ የኢኖቬሽን፣ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ ከላሊ አድሀና(ዶ/ር) ናቸው።
ለሁለንተናዊ እድገት ሁለንተናዊ ጥናትና ምርምር ማካሄድ እንዲሁም መሰል የምክክር መድረኮችን አጠናክሮ ማስቀጠል የተጀመሩ ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ እንደሚረዱም የውይይቱ ተሳታፊዎች አመልክተዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026