
መቀሌ፤ የካቲት 10/2017(ኢዜአ)፡- በትግራይ ክልል ዘላቂ ሰላምን በማስፈንና እምቅ የሆነውን የተፈጥሮ ሃብት በማልማት የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ተገልጿል።
የክልሉ ኢኮኖሚ ያለበትን ሁኔታ እና ማተኮር በሚገቡ አቅጣጫዎችን የተመለከተ ፎረም በመቀሌ ተካሂዷል።
በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የፖሊሲ ጥናትና ምርምር ኢንስቲትዩት ከፍተኛ ተመራማሪ ካህሳይ በርሄ(ዶ/ር) የውይይት መነሻ ፅሑፍ ባቀረቡበት ወቅት እንዳሉት፤ የክልሉን ኢንቨስትመንት እና ኢኮኖሚ ለማሳደግ ምቹ ሁኔታን መፍጠር እና ሰላምን ማጠናከር ይገባል።

ክልሉ የበርካታ ፀጋዎች ባለቤት መሆኑን ጠቁመው በተለይ በግብርና፣ በማዕድንና በቱሪዝም ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን በአግባቡ ጥቅም ላይ ለማዋል ሰላምና መረጋጋትን ማጠናከር ወሳኝ ነው ብለዋል።
በአጠቃላይ የክልሉን ኢኮኖሚ ለማሳደግ የሲቪል ሰርቫንቱን ጨምሮ የአሰራርና የተቋማት ሪፎርም ትግበራዎችን ማከናወን አስፈላጊ እንደሆነም ጨምረው አመላክተዋል።
በኢንስቲትዩቱ የኢኮኖሚ ምሁር አርዓያ መብራህቱ(ዶ/ር) በበኩላቸው የክልሉን ኢኮኖሚ ለማሳደግ የግብርና፣ የኢንዱስትሪ እና የአገልግሎት ዘርፎች ትኩረት ሊሰጣቸው ይገባል ብለዋል።
በፌዴራል መንግስት እየተደረጉ ያሉ ድጋፎች መጠናከር ወሳኝ መሆኑን አንስተው የክልሉን እምቅ ሃብት የማልማትና የመጠቀም ስራ ሊጠናከር ይገባል ነው ያሉት።
የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ለማስቀጠልና የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከምንም በላይ የክልሉን ሰላም ለማፅናት በትብብርና በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባም ተናግረዋል።
በክልሉ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም፣ የማህበራዊ ትስስርና የአስተሳሰብ ለውጥ ማምጣት አለብን ያሉት ደግሞ በጊዜያዊ አስተዳደሩ የኢኖቬሽን፣ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ ከላሊ አድሀና(ዶ/ር) ናቸው።
ለሁለንተናዊ እድገት ሁለንተናዊ ጥናትና ምርምር ማካሄድ እንዲሁም መሰል የምክክር መድረኮችን አጠናክሮ ማስቀጠል የተጀመሩ ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ እንደሚረዱም የውይይቱ ተሳታፊዎች አመልክተዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026