ደሴ፤ የካቲት 11/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተመደበው በጀት ለታለመለት ዓላማ እንዲውል የተጠናከረ ክትትል፣ ቁጥጥርና ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ገንዘብ ቢሮ አስታወቀ፡፡
ቢሮው የ2017 ዓ.ም የስድስት ወራት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በደሴ ከተማ እያካሄደ ነው፡፡
በመድረኩ የቢሮው ኃላፊ ጥላሁን መሃሪ(ዶ/ር) እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ከ150 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት በምክር ቤቱ በማጸደቅ ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡
የተመደበው በጀት ለታለመለት ዓላማ ጥቅም ላይ እንዲውል የተጠናከረ ክትትል፣ ቁጥጥርና ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በክትትልና ቁጥጥሩም ባለፉት ዓመታት በበጀት አጠቃቀም ዙሪያ ይሰተዋሉ የነበሩ ችግሮች መሻሻላቸውን ተናግረዋል፡፡
ከተመደበው በጀት እስካሁን ከ32 ቢሊዮን ብር በላይ ጥቅም ላይ መዋሉን የተናገሩት የቢሮ ኃላፊው በክልሉ 79 በመቶ ውዝፍ የኦዲት ግኝትም እንዲመለስ መደረጉን ገልጸዋል፡፡
በመድረኩ የክልል፣ የዞንና የወረዳ አመራር አባላትን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025