የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>በአማራ ክልል የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ የተመደበው በጀት ለታለመለት አላማ እንዲውል ቁጥጥር እየተደረገ ነው</p>

Feb 19, 2025

IDOPRESS

ደሴ፤ የካቲት 11/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተመደበው በጀት ለታለመለት ዓላማ እንዲውል የተጠናከረ ክትትል፣ ቁጥጥርና ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ገንዘብ ቢሮ አስታወቀ፡፡

ቢሮው የ2017 ዓ.ም የስድስት ወራት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በደሴ ከተማ እያካሄደ ነው፡፡


በመድረኩ የቢሮው ኃላፊ ጥላሁን መሃሪ(ዶ/ር) እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ከ150 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት በምክር ቤቱ በማጸደቅ ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡

የተመደበው በጀት ለታለመለት ዓላማ ጥቅም ላይ እንዲውል የተጠናከረ ክትትል፣ ቁጥጥርና ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በክትትልና ቁጥጥሩም ባለፉት ዓመታት በበጀት አጠቃቀም ዙሪያ ይሰተዋሉ የነበሩ ችግሮች መሻሻላቸውን ተናግረዋል፡፡

ከተመደበው በጀት እስካሁን ከ32 ቢሊዮን ብር በላይ ጥቅም ላይ መዋሉን የተናገሩት የቢሮ ኃላፊው በክልሉ 79 በመቶ ውዝፍ የኦዲት ግኝትም እንዲመለስ መደረጉን ገልጸዋል፡፡

በመድረኩ የክልል፣ የዞንና የወረዳ አመራር አባላትን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው &quot;ቡኖ - ማላ&quot; ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026