የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ ተግባራዊ በተደረጉ የልማት ውጥኖች ተስፋ ሰጪ ውጤቶች ተገኝተዋል</p>

Feb 19, 2025

IDOPRESS

ሮቤ፤ የካቲት 11/2017(ኢዜአ)፡- በባሌ ዞን ባለፉት ዓመታት በግብርናው ዘርፍ ተግባራዊ በተደረጉ የልማት ኢኒሼቲቮች ተስፋ ሰጪ ውጤቶች ማስገኘታቸውን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብዱልሐኪም አልይ ገለጹ።

አቶ አብዱልሐኪም አልይ ለኢዜአ እንዳሉት በዞኑ ባለፉት ዓመታት በኦሮሚያ ክልል መንግስት በተቀረጹ የግብርና ልማት ኢኒሼቲቮች ተስፋ ሰጪ ውጤቶች ተመዝግቧል።

በዞኑ ስንዴን በክላስተር ማልማት፣ በአትክልትና ፍራፍሬ፣ በዶሮ እርባታ፣ በንብ ማነብ እንዲሁም በቡና ልማት ዘርፍ አርሶ አደሩ የተሻለ ውጤት ያገኘባቸው ዋና ዋና ኢኒሼቲቮች መሆናቸውን ተናግረዋል።

በተለይ አርሶ አደሩ በኩታ ገጠም አሰራር ዘዴ ውጤታማ በሆነ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸው በዚህም የምግብ ዋስትናውን ከማረጋገጥ ባሻገር ገቢውም እንዲያድግ እያገዘው ነው ብለዋል።

በዞኑ በመኽሩ ወቅት ከ580ሺህ ሄክታር የሚበልጥ መሬት የተሻሻሉ የግብርና አሰራሮችን ተግባራዊ በማድረግ መልማቱን አስታውሰዋል።

ከዚህ መካከል 250ሺህ ሄክታር መሬት የተሻሻለ የግብርና አሰራርና በመተግበር በስንዴ የለማ መሆኑን ጠቁመው ከ16 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱንም በማሳያነት አቅርበዋል።

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በዚህ ዓመት ብቻ ከ110ሺህ የሚበልጡ ላሞችን በሰው ሰራሽ ዘዴ ለማዳቀል እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።

ባለፉት ዓመታት የተፈጥሮ ኃብት ልማት ሥራ የተከናወኑባቸው አካባቢዎች ወጣቶችንና አርሶ አደሩን በማህበራት በማደራጀት በማር ምርት ኢኒሼቲቭ እንዲሰማሩ ከ85ሺህ የሚበልጡ ዘመናዊ ቀፎዎች ተሰራጭተዋል ብለዋል።

ከበጋ መስኖ ልማት አንጻርም በዞኑ 188ሺህ ሄክታር መሬት የማልማት ስራው በስፋት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

የተጀመረው ስራ ወጥነት ባለው መልኩ በሁሉም አርሶ አደሮች ተግባራዊ እንዲደረግ የግብርና ባለሙያው በንቃት እንዲሳተፍ ይደረጋል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026