
ሮቤ፤ የካቲት 11/2017(ኢዜአ)፡- በባሌ ዞን ባለፉት ዓመታት በግብርናው ዘርፍ ተግባራዊ በተደረጉ የልማት ኢኒሼቲቮች ተስፋ ሰጪ ውጤቶች ማስገኘታቸውን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብዱልሐኪም አልይ ገለጹ።
አቶ አብዱልሐኪም አልይ ለኢዜአ እንዳሉት በዞኑ ባለፉት ዓመታት በኦሮሚያ ክልል መንግስት በተቀረጹ የግብርና ልማት ኢኒሼቲቮች ተስፋ ሰጪ ውጤቶች ተመዝግቧል።
በዞኑ ስንዴን በክላስተር ማልማት፣ በአትክልትና ፍራፍሬ፣ በዶሮ እርባታ፣ በንብ ማነብ እንዲሁም በቡና ልማት ዘርፍ አርሶ አደሩ የተሻለ ውጤት ያገኘባቸው ዋና ዋና ኢኒሼቲቮች መሆናቸውን ተናግረዋል።
በተለይ አርሶ አደሩ በኩታ ገጠም አሰራር ዘዴ ውጤታማ በሆነ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸው በዚህም የምግብ ዋስትናውን ከማረጋገጥ ባሻገር ገቢውም እንዲያድግ እያገዘው ነው ብለዋል።
በዞኑ በመኽሩ ወቅት ከ580ሺህ ሄክታር የሚበልጥ መሬት የተሻሻሉ የግብርና አሰራሮችን ተግባራዊ በማድረግ መልማቱን አስታውሰዋል።
ከዚህ መካከል 250ሺህ ሄክታር መሬት የተሻሻለ የግብርና አሰራርና በመተግበር በስንዴ የለማ መሆኑን ጠቁመው ከ16 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱንም በማሳያነት አቅርበዋል።
በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በዚህ ዓመት ብቻ ከ110ሺህ የሚበልጡ ላሞችን በሰው ሰራሽ ዘዴ ለማዳቀል እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።
ባለፉት ዓመታት የተፈጥሮ ኃብት ልማት ሥራ የተከናወኑባቸው አካባቢዎች ወጣቶችንና አርሶ አደሩን በማህበራት በማደራጀት በማር ምርት ኢኒሼቲቭ እንዲሰማሩ ከ85ሺህ የሚበልጡ ዘመናዊ ቀፎዎች ተሰራጭተዋል ብለዋል።
ከበጋ መስኖ ልማት አንጻርም በዞኑ 188ሺህ ሄክታር መሬት የማልማት ስራው በስፋት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
የተጀመረው ስራ ወጥነት ባለው መልኩ በሁሉም አርሶ አደሮች ተግባራዊ እንዲደረግ የግብርና ባለሙያው በንቃት እንዲሳተፍ ይደረጋል ብለዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026