
አዳማ፤ የካቲት 11/ 2017(ኢዜአ)፡- በአዳማ ከተማ የህብረተሰቡ የቁጠባ ባህል እንዲጎለብትና የፋይናንስ አቅርቦት ችግሮችን ለመፍታት ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አቶ ሃይሉ ጀልዴ ገለፁ።
አስተዳደሩ የቁጠባ ባህል ለማሳደግ የጥቃቅንና አነስተኛ እንዲሁም የኢንተርፕርነሮችን የፋይናንስ አቅርቦት ችግር ለመፍታት ከሲንቄ ባንክ ጋር በትብብር ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።
የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሃይሉ ጀልዴ በዚህ ወቅት እንደገለፁት የህብረተሰቡ የቁጠባ ባህል እንዲጎለብትና የስራ ባህል እንዲለወጥ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ።
በተለይ የከተማው ነዋሪ ሰርቶ መለወጥ እንዲችል ኢንተርፕርነርሽፕና የስራ ዕድል ፈጠራ ላይ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።
የአገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን የልማት ስራዎችን ለማፋጠን ትኩረት መሰጠቱን ጠቅሰው
የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ሰራተኞች የስራ ባህልና አስተሳሰብ መለወጥ እንደሚገባም አክለዋል።
የቁጠባ ባህልን በማሳደግ በመቆጠብ ወደ ስራ መግባትና ራሳን መለወጥ እንዲቻል ከባንኩ ጋር ስምምነት መፈረሙን ገልጸዋል።
ተጠቃሚው ብድሩን በወቅቱ እንዲመልስ በየደረጃው የሚገኘው ባለድርሻ አካላትና አመራሮች በቅንጅት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበው አስተዳደሩ ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር መስራቱን ይቀጥላል ብለዋል።
የሲንቄ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ ነዋይ መገርሳ በበኩላቸው ባንኩ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ቢሆንም አርሶ አደሩንና አርብቶ አደሩን ጨምሮ የገጠሩን ማህበረሰብ በማቀፍ አመርቂ ለውጥ እያመጣ ይገኛል ነው ያሉት።
የህዝቡ የቁጠባ ባህል እንዲጎለብትና ብድር ወስዶ ተጠቃሚ በመሆን በወቅቱ መመለስ እንዲችል በየደረጃው ክትትል መደረግ አለበት ሲሉም ገልጸዋል።
ባንኩ የፋይናንስ አቅርቦት ችግርን በመቅረፍ በስራ ዕድል ፈጠራ፤ በሊዝ ማሽን አቅርቦት፤ በኢንቨስትመንት ላይ በትኩረት እየሰራ ነው ብለዋል።
ድህነትንና ስራ አጥነትን ለመቀነስ የሚደረገውን ጥረት ባንኩ ድጋፉን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026