የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>በአዳማ ከተማ የህብረተሰቡ የቁጠባ ባህል እንዲጎለብትና የፋይናንስ አቅርቦት ችግሮችን ለመፍታት ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ ነው</p>

Feb 19, 2025

IDOPRESS

አዳማ፤ የካቲት 11/ 2017(ኢዜአ)፡- በአዳማ ከተማ የህብረተሰቡ የቁጠባ ባህል እንዲጎለብትና የፋይናንስ አቅርቦት ችግሮችን ለመፍታት ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አቶ ሃይሉ ጀልዴ ገለፁ።

አስተዳደሩ የቁጠባ ባህል ለማሳደግ የጥቃቅንና አነስተኛ እንዲሁም የኢንተርፕርነሮችን የፋይናንስ አቅርቦት ችግር ለመፍታት ከሲንቄ ባንክ ጋር በትብብር ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።

የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሃይሉ ጀልዴ በዚህ ወቅት እንደገለፁት የህብረተሰቡ የቁጠባ ባህል እንዲጎለብትና የስራ ባህል እንዲለወጥ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ።

በተለይ የከተማው ነዋሪ ሰርቶ መለወጥ እንዲችል ኢንተርፕርነርሽፕና የስራ ዕድል ፈጠራ ላይ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።

የአገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን የልማት ስራዎችን ለማፋጠን ትኩረት መሰጠቱን ጠቅሰው

የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ሰራተኞች የስራ ባህልና አስተሳሰብ መለወጥ እንደሚገባም አክለዋል።

የቁጠባ ባህልን በማሳደግ በመቆጠብ ወደ ስራ መግባትና ራሳን መለወጥ እንዲቻል ከባንኩ ጋር ስምምነት መፈረሙን ገልጸዋል።

ተጠቃሚው ብድሩን በወቅቱ እንዲመልስ በየደረጃው የሚገኘው ባለድርሻ አካላትና አመራሮች በቅንጅት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበው አስተዳደሩ ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር መስራቱን ይቀጥላል ብለዋል።

የሲንቄ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ ነዋይ መገርሳ በበኩላቸው ባንኩ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ቢሆንም አርሶ አደሩንና አርብቶ አደሩን ጨምሮ የገጠሩን ማህበረሰብ በማቀፍ አመርቂ ለውጥ እያመጣ ይገኛል ነው ያሉት።

የህዝቡ የቁጠባ ባህል እንዲጎለብትና ብድር ወስዶ ተጠቃሚ በመሆን በወቅቱ መመለስ እንዲችል በየደረጃው ክትትል መደረግ አለበት ሲሉም ገልጸዋል።

ባንኩ የፋይናንስ አቅርቦት ችግርን በመቅረፍ በስራ ዕድል ፈጠራ፤ በሊዝ ማሽን አቅርቦት፤ በኢንቨስትመንት ላይ በትኩረት እየሰራ ነው ብለዋል።

ድህነትንና ስራ አጥነትን ለመቀነስ የሚደረገውን ጥረት ባንኩ ድጋፉን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026