ወልቂጤ፤ የካቲት 12/2017(ኢዜአ)፡- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከመኸር እርሻ ከ44 ነጥብ 9 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) ገለጹ።
በበጋ ወቅት መደበኛ የመስኖ ልማት ሥራም በክልሉ ከ146 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱም ተመላክቷል።
ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) የክልሉን የአስፈፃሚ ተቋማት የስድስት ወራት ሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ዛሬ ለክልሉ ምክር ቤት አቅርበዋል።
በሪፖርቱም በክልሉ የመኸር እርሻ ወቅት ከ557 ሺህ 230 ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች መልማቱን ገልጽዋል።
በዚህም ከ44 ነጥብ 9 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መቻሉን ተናግረዋል።
የክልሉን የግብርና አቅም አሟጦ በመጠቀም የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት ለማሳካትና ዘርፉ ለሥራ ዕድል ፈጠራ ጉለህ አስተዋጽኦ እንዲኖረው በቅንጅት መሰራቱን ተናግረዋል።
ምርታማነትን ለማሳደግ ለግብአትና ለቴክኖሎጂ አቅርቦትና አጠቃቀም ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ድጋፍና ክትትል ሲደረግ መቆየቱን አስታውሰው፣ በተሰራው ሥራ የተገኘው ውጤት ገበያን ለማረጋጋት እያገዘ ነው ብለዋል።
በክልሉ ግብርናን ለማሳደግ የተጀመረው ቅንጅታዊ ጥረት በአዳዲስ እሳቤዎች ተጠናክሮ ይቀጥላል ነው ያሉት።
አሁን ላይ በበጋ ወቅት በሚከናወን መደበኛ መስኖ ልማት ከ146 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ ምዕራፍ መገባቱንም አንስተዋል።
ክልሉ ያለውን የገቢ አማራጭ አሟጦ በመሰብሰብ የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄ ለመፍታት በተደረገ እንቅስቃሴም ከ6 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን ጠቁመው፣ ይህም ካለፈው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር 39 በመቶ ብልጫ እንዳለው ገልጸዋል።
በግማሽ በጀት ዓመቱ በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ከ215 ሺህ በላይ ዜጎችን በጊዜያዊና ቋሚ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏልም ነው ያሉት።
በትምህርት ዘርፍ የተማሪዎችን ውጤት ማሻሻል የሚያችል የትምህርት ቤቶች ደረጃ የማሻሻል ሥራን ጨምሮ የግብአትና የመምህራን አቅም ግንባታ ሥራዎች መከናወናቸውንም ተናግረዋል።
በጤናው ዘርፍም በሽታን መከላከልን መሰረት ባደረገ መልኩ ሥራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን ጠቅሰው፣ በተለይ የሕክምና አገልግሎት ተደራሽነት ላይ ውጤታማ ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።
በግማሽ በጀት ዓመቱ በኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ዘርፎች በክልሉ አበረታች ሥራዎች መከናወናቸውን ርዕሰ መስተዳድሩ አስታውቀዋል።
የምክር ቤቱ አባላትም በሪፖርቱ ላይ ያላቸውን ጥያቄና አስተያየት በማቅረብ ላይ ናቸው።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025