
ደሴ ፤ የካቲት 12/2017(ኢዜአ)፡-በደሴ እየተከናወኑ የሚገኙ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች የከተማዋን ዕድገት በማፋጠን የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያጎለብቱ መሆናቸው ተገለጸ።
የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ፈንታ ደጀን በደሴ ከተማ የተለያዩ የልማት እንቅስቃሴዎችን ዛሬ ጎብኝተዋል፡፡
ሚኒስትር ዴኤታው በወቅቱ እንደተናገሩት፤ ከተሞችን ለነዋሪዎች ምቹ፣ የኢንቨስትመንትና የኢኮኖሚ ምንጭ ለማድረግ እየተሰራ ነው፡፡

ከዚህ አንጻር በደሴ የተከናወኑና በመከናወን ላይ ያሉ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች የከተማውን እድገት የሚያፋጥኑ በመሆናቸው የሚበረታቱና ተጠናክረው መቀጠል ያለባቸው ናቸው ብለዋል፡፡
የ"ኦን ላይን" አገልግሎት፣ "ስማርት ሲቲ" ፣ የአስፋልት መንገድ፣ የአውቶቡስ መናኸሪያ ፣ ኮሪደር ልማትና ሌሎችም በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዙ ተግባራት በከተማው መመልከታቸውን ጠቅሰዋል።
ይህም ከተሞችን ለማሳደግና ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ መንግስት ያስቀመጠው አቅጣጫ በትክክለኛው መንገድ ስለመተግበሩ ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል።
በከተሞች የሚገነቡ መሰረተ ልማቶችን በቴክኖሎጂ ዲጅታላይዝድ በማድረግ ለህጻናትና ለአረጋዊያንም ጭምር ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር በትኩረት መስራት እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡

በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የደሴ ከተማ አስተዳደር የከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ቃሲም አበራ በበኩላቸው፤ በከተማው የመሰረተ ልማትን በማሟላት ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
በስማርት ሲቲ፣ በኮሪደር እና በሌሎችም መሰረተ ልማቶች አበረታች ውጤት መመዝገቡን ጠቁመው፤ የፌዴራልና የክልሉ መንግስት የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንዲቀጥሉም አመልክተዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026