
ደሴ ፤ የካቲት 12/2017(ኢዜአ)፡-በደሴ እየተከናወኑ የሚገኙ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች የከተማዋን ዕድገት በማፋጠን የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያጎለብቱ መሆናቸው ተገለጸ።
የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ፈንታ ደጀን በደሴ ከተማ የተለያዩ የልማት እንቅስቃሴዎችን ዛሬ ጎብኝተዋል፡፡
ሚኒስትር ዴኤታው በወቅቱ እንደተናገሩት፤ ከተሞችን ለነዋሪዎች ምቹ፣ የኢንቨስትመንትና የኢኮኖሚ ምንጭ ለማድረግ እየተሰራ ነው፡፡

ከዚህ አንጻር በደሴ የተከናወኑና በመከናወን ላይ ያሉ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች የከተማውን እድገት የሚያፋጥኑ በመሆናቸው የሚበረታቱና ተጠናክረው መቀጠል ያለባቸው ናቸው ብለዋል፡፡
የ"ኦን ላይን" አገልግሎት፣ "ስማርት ሲቲ" ፣ የአስፋልት መንገድ፣ የአውቶቡስ መናኸሪያ ፣ ኮሪደር ልማትና ሌሎችም በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዙ ተግባራት በከተማው መመልከታቸውን ጠቅሰዋል።
ይህም ከተሞችን ለማሳደግና ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ መንግስት ያስቀመጠው አቅጣጫ በትክክለኛው መንገድ ስለመተግበሩ ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል።
በከተሞች የሚገነቡ መሰረተ ልማቶችን በቴክኖሎጂ ዲጅታላይዝድ በማድረግ ለህጻናትና ለአረጋዊያንም ጭምር ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር በትኩረት መስራት እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡

በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የደሴ ከተማ አስተዳደር የከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ቃሲም አበራ በበኩላቸው፤ በከተማው የመሰረተ ልማትን በማሟላት ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
በስማርት ሲቲ፣ በኮሪደር እና በሌሎችም መሰረተ ልማቶች አበረታች ውጤት መመዝገቡን ጠቁመው፤ የፌዴራልና የክልሉ መንግስት የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንዲቀጥሉም አመልክተዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026