
አዲስ አበባ ፤የካቲት 13/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሀገራቱ መካከል ያለውን የኢንቨስትመንት ፍሰት መጠን ለማሳደግ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) በሩሲያ ኢኮኖሚ ሚኒስትር ማክሲም ራሽቲኒኮቭ ከተመራ ከፍተኛ ልዑካን ቡድን ጋር በጽህፈት ቤታቸው ተወያይተዋል።
ኮሚሽነር ዘለቀ፥ መንግስት የግሉን ዘርፍ ለማሳደግ እና ምቹ የኢንቨስትመንት ከባቢ ለመፍጠር እየተገበራቸው ያሉ ሪፎርሞች እና ኢንቨስትመንት ለማስፋፋት እያደረጋቸው የሚገኙ ጥረቶችን አስመልክቶ ለልዑኩ ገለጻ አድርገዋል።
ኮሚሽነሩ የኢትዮጵያ መንግስት የኢትዮጵያ እና የሩሲያ ረጅም ጊዜ ያስቆጠረ ሁለንተናዊ ግንኙነት በኢኮኖሚያዊና የመዋዕለ ነዋይ ፍሰት ዘርፍ እንዲያድግ ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸዋል።
የሩስያ ኢኮኖሚ ሚኒስትር ማክሲም ራሽቲኒኮቭ ሀገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር በኢኮኖሚ እና በግሉ ዘርፍ ኢንቨስትመንት ያላትን ትብብር ለማሳደግ ፍላጎት አላት ብለዋል።
ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በማዕድን ሀብት ልማት፣ በአፈር ማዳበሪያ ምርት፣ በታዳሽ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት እና ማሰራጨት፣ የመረጃና ቴክኖሎጂ ዘርፎችና የልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች ማዘመንን ጨምሮ በሌሎች ዘርፎች ላይ በትብብር ለመስራት ከስምምነት ላይ ደርሰዋል።
ሀገራቱ በጋራ ሊያለሟቸው የሚችሏቸውን የኢንቨስትመንት ዘርፎችና ፕሮጀክቶችን በጋራ ለመለየት የሚያስችል የኢንቨስትመንት እና ቢዝነስ ፎረሞችን በቀጣይነት በጋራ እንደሚያካሂዱ መግለጻቸውን ከኮሚሽኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026