
አዲስ አበባ ፤የካቲት 13/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሀገራቱ መካከል ያለውን የኢንቨስትመንት ፍሰት መጠን ለማሳደግ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) በሩሲያ ኢኮኖሚ ሚኒስትር ማክሲም ራሽቲኒኮቭ ከተመራ ከፍተኛ ልዑካን ቡድን ጋር በጽህፈት ቤታቸው ተወያይተዋል።
ኮሚሽነር ዘለቀ፥ መንግስት የግሉን ዘርፍ ለማሳደግ እና ምቹ የኢንቨስትመንት ከባቢ ለመፍጠር እየተገበራቸው ያሉ ሪፎርሞች እና ኢንቨስትመንት ለማስፋፋት እያደረጋቸው የሚገኙ ጥረቶችን አስመልክቶ ለልዑኩ ገለጻ አድርገዋል።
ኮሚሽነሩ የኢትዮጵያ መንግስት የኢትዮጵያ እና የሩሲያ ረጅም ጊዜ ያስቆጠረ ሁለንተናዊ ግንኙነት በኢኮኖሚያዊና የመዋዕለ ነዋይ ፍሰት ዘርፍ እንዲያድግ ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸዋል።
የሩስያ ኢኮኖሚ ሚኒስትር ማክሲም ራሽቲኒኮቭ ሀገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር በኢኮኖሚ እና በግሉ ዘርፍ ኢንቨስትመንት ያላትን ትብብር ለማሳደግ ፍላጎት አላት ብለዋል።
ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በማዕድን ሀብት ልማት፣ በአፈር ማዳበሪያ ምርት፣ በታዳሽ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት እና ማሰራጨት፣ የመረጃና ቴክኖሎጂ ዘርፎችና የልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች ማዘመንን ጨምሮ በሌሎች ዘርፎች ላይ በትብብር ለመስራት ከስምምነት ላይ ደርሰዋል።
ሀገራቱ በጋራ ሊያለሟቸው የሚችሏቸውን የኢንቨስትመንት ዘርፎችና ፕሮጀክቶችን በጋራ ለመለየት የሚያስችል የኢንቨስትመንት እና ቢዝነስ ፎረሞችን በቀጣይነት በጋራ እንደሚያካሂዱ መግለጻቸውን ከኮሚሽኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026