ደ

ሴ የካቲት 13/2017 (ኢዜአ)፡- የመንግስት የኤሌክትሮኒክስ ግዥ ስርዓት ግልጽ፣ ፈጣንና ቀልጣፋ የግዥ አሰራር መፍጠሩን የፌዴራል መንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር መሰረት መስቀሌ ተናገሩ።
ባለስልጣኑ ከወሎ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በመንግስት የኤሌክትሮኒክስ ግዥ ስርዓት አጠቃቀምና አሰራር ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል።
በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር መሰረት መስቀሌ፤ የግዥ ስርዓቱን ዲጅታላይዝድ በማድረግ ፈጣን፣ ግልጽና ፍትሃዊ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።፡
ለዚህም በፌዴራል የመንግስት መስሪያ ቤቶችና ተቋማት የኤሌክትሮኒክስ ግዥ ስርዓት ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል ነው ያሉት።
በአሰራሩ ቀደም ሲል ይስተዋሉ የነበሩ ብልሹ አሰራሮችን በማስቀረት ግልጽ፣ ፈጣንና ቀልጣፋ የግዥ አገልግሎት እየተሰጠ ይገኛል ብለዋል።
የወሎ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት አወል ሰይድ (ዶ/ር)፤ የኤሌክትሮኒክስ ግዥ ስርዓቱ የሀገርን በጀት በአግባቡ ጥቅም ላይ ለማዋል እንዲሁም ለመንግስታዊ አሰራር ግልጸኝነትና ለንግዱ ማህበረሰብ ጭምር የላቀ ሚና ያለው መሆኑን አንስተዋል።

የግዥ ስርአቱ በተለይም በዩኒቨርሲቲዎች ያለውን የግዥ ስርዓት ከብዙ ውስብስብ ችግሮች ያስወጣ ስለመሆኑም ገልጸዋል።
በመሆኑም በአቅራቢ ነጋዴዎች ወደ ሲስተሙ በመግባት ተወዳዳሪና ተጠቃሚ ለመሆን መዘጋጀት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

በስልጠናው በርካታ ነጋዴዎች፣ የዩኒቨርሲቲው አመራሮችና የግዥ ባለሙያዎችን ጨምሮ ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026