ደ

ሴ የካቲት 13/2017 (ኢዜአ)፡- የመንግስት የኤሌክትሮኒክስ ግዥ ስርዓት ግልጽ፣ ፈጣንና ቀልጣፋ የግዥ አሰራር መፍጠሩን የፌዴራል መንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር መሰረት መስቀሌ ተናገሩ።
ባለስልጣኑ ከወሎ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በመንግስት የኤሌክትሮኒክስ ግዥ ስርዓት አጠቃቀምና አሰራር ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል።
በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር መሰረት መስቀሌ፤ የግዥ ስርዓቱን ዲጅታላይዝድ በማድረግ ፈጣን፣ ግልጽና ፍትሃዊ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።፡
ለዚህም በፌዴራል የመንግስት መስሪያ ቤቶችና ተቋማት የኤሌክትሮኒክስ ግዥ ስርዓት ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል ነው ያሉት።
በአሰራሩ ቀደም ሲል ይስተዋሉ የነበሩ ብልሹ አሰራሮችን በማስቀረት ግልጽ፣ ፈጣንና ቀልጣፋ የግዥ አገልግሎት እየተሰጠ ይገኛል ብለዋል።
የወሎ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት አወል ሰይድ (ዶ/ር)፤ የኤሌክትሮኒክስ ግዥ ስርዓቱ የሀገርን በጀት በአግባቡ ጥቅም ላይ ለማዋል እንዲሁም ለመንግስታዊ አሰራር ግልጸኝነትና ለንግዱ ማህበረሰብ ጭምር የላቀ ሚና ያለው መሆኑን አንስተዋል።

የግዥ ስርአቱ በተለይም በዩኒቨርሲቲዎች ያለውን የግዥ ስርዓት ከብዙ ውስብስብ ችግሮች ያስወጣ ስለመሆኑም ገልጸዋል።
በመሆኑም በአቅራቢ ነጋዴዎች ወደ ሲስተሙ በመግባት ተወዳዳሪና ተጠቃሚ ለመሆን መዘጋጀት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

በስልጠናው በርካታ ነጋዴዎች፣ የዩኒቨርሲቲው አመራሮችና የግዥ ባለሙያዎችን ጨምሮ ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026