የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>የመንግስት የኤሌክትሮኒክስ ግዥ ስርዓት ግልጽ፣ ፈጣንና ቀልጣፋ የግዥ አሰራር ፈጥሯል</p>

Feb 21, 2025

IDOPRESS


ሴ የካቲት 13/2017 (ኢዜአ)፡- የመንግስት የኤሌክትሮኒክስ ግዥ ስርዓት ግልጽ፣ ፈጣንና ቀልጣፋ የግዥ አሰራር መፍጠሩን የፌዴራል መንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር መሰረት መስቀሌ ተናገሩ።

ባለስልጣኑ ከወሎ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በመንግስት የኤሌክትሮኒክስ ግዥ ስርዓት አጠቃቀምና አሰራር ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል።

በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር መሰረት መስቀሌ፤ የግዥ ስርዓቱን ዲጅታላይዝድ በማድረግ ፈጣን፣ ግልጽና ፍትሃዊ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።፡

ለዚህም በፌዴራል የመንግስት መስሪያ ቤቶችና ተቋማት የኤሌክትሮኒክስ ግዥ ስርዓት ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል ነው ያሉት።

በአሰራሩ ቀደም ሲል ይስተዋሉ የነበሩ ብልሹ አሰራሮችን በማስቀረት ግልጽ፣ ፈጣንና ቀልጣፋ የግዥ አገልግሎት እየተሰጠ ይገኛል ብለዋል።

የወሎ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት አወል ሰይድ (ዶ/ር)፤ የኤሌክትሮኒክስ ግዥ ስርዓቱ የሀገርን በጀት በአግባቡ ጥቅም ላይ ለማዋል እንዲሁም ለመንግስታዊ አሰራር ግልጸኝነትና ለንግዱ ማህበረሰብ ጭምር የላቀ ሚና ያለው መሆኑን አንስተዋል።


የግዥ ስርአቱ በተለይም በዩኒቨርሲቲዎች ያለውን የግዥ ስርዓት ከብዙ ውስብስብ ችግሮች ያስወጣ ስለመሆኑም ገልጸዋል።

በመሆኑም በአቅራቢ ነጋዴዎች ወደ ሲስተሙ በመግባት ተወዳዳሪና ተጠቃሚ ለመሆን መዘጋጀት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።


በስልጠናው በርካታ ነጋዴዎች፣ የዩኒቨርሲቲው አመራሮችና የግዥ ባለሙያዎችን ጨምሮ ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026